የኢትዮ ሱዳን ድንበር በሕገወጥነት ከሕዝብ ፈቃድ ውጪ መካለልን በመቃወም በዲሲ ሰልፍ ተደረገ::


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


የወያኔ አገዛዝ ለወዳጁ የሱዳን መንግስት ከኢትዮጵያ ድንበር ቆርሶ ለመስጠት ደፋ ቀና እያለ ባለበት በዚህ ወቅት ይህንን የድንበር መካለል በመቃወም በዋሽንግተን ዲሲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በሱዳን ኤምባሲ ደጃፍ የተቃውሞ ድምጻቸው አሰሙ:: ሱዳን ሰላም ከፈለግሽ ዛሬ ከወያኔ ጋር የምታደርጊውን የድብቅ የድንበር ውል ማቆም አለብሽ ለድንበራችን ህይወት እንገብራ አንፈራም በማለት ሰልፈኛው ቁጣውን ገልጿል::


በሰልፉ ላይ የኦሮሞ ዲሞክራቲክ ግንባር የዲሲ ግብረሃይል እና የሞረሽ ወገኔ ትወካዮች ንግግር አድርገዋል::
ድንበሩ ሲካለል ከ1200 ኪሎ ሜትር በላይ ግዛት እንዲሁም አፄ ቴድሮስ የተማሩበት የቋራው ገዳም እና አፄ ዮሃንስ የተሰዉበት የመተማ ከተማ ለሱዳን ተላልፎ ይሰጣል::#MinilikSalsawi