ይህ መንግስት ምን ይዞ ቆመ ( ኄኖክ የሺጥላ )


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


ሰሞኑን በአምቦ ፣ በሐረማያ ፣ በወለጋ ፣ በቡራዩ እና ወዘተ ቦታዎች ኢትዮጵያውያኖች ዛሬም በዘረኛው ወያኔ ትግሬ እየተገደሉ እንደሆነ ሰምቻለሁ ። በጎንደር ኢትዮጵያውያኖች እየተገደሉ እንደሆነ ሰምቻለሁ ። ህዝበ ሙስሊሙ የእምነት ነጻነቱን እንደተነጠቀም አውቃለሁ ። አስራምስት ሚሊዮን ሕዝብ አፋጣኝ የምግብ እርዳታ በሚሻበት ሁኔታ ላይም እንደሆነ ተረድቻለሁ ፣ በምራብ ጎጃም ንጹሃን ዜጎች እየተሰቃዩ እንደሆነም መረጃ አለኝ ፣ በወሎ ( ኮረም ) ፣ በ ወልቃይት ጠገዴ ፣ ሁመራ እና ወዘተ ህዝቡ አዲስ የተሰጠውን ማንነት አልቀበልም ብሎ ከመንግስት ጋ ግብ ግብ ውስጥ እንዳለም እናውቃለን ፣ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያን መንግስትን ( ስርዓቱን ) በመተቸታቸው በቃሊቲ ፣ ቂሊንጦ እና መሰል እስ ቤቶች እንደተታጎሩ ከማንም የተደበቀ ሚስጥር አይደለም ፣ ሰማያዊ ፣ አንድነት እና መድረክ ድምጻቸው ተገሶ ፣ መንግስት 100% እንደተመረጠ እንደተናገረም ሰምተናል ። ታዲያ ያልገባኝ ይሄን መንግስት ” ምን ይሆን ቆሞ እንዲሄድ ያድረገው ?” ከነዚህ ሁሉ ብጥብጦች እና መከራዎች ጀረባ የትግራይ ሕዝብ ሚና ምንድን ነው የሚለውን በጥሞና እንመርምር ። ከትግራይ በስተቀር በሁሉም አቅጣጫ ኢትዮጵያውያኖች ይገደላሉ ፣ ይህ በየትኛውም አይነት ስርዓት ያልሆነ ነው ። ለምሳሌ ወያኔ ያማራ ስርዓት የሚለው ደርግ ፣ በኢሕአፓ ስም የበላው የጎንደር ትውልድ ( ሕዝብ ) አንዱ ምሳሌ ነው ።

ስለዚህ ሁኔታውን ከይሉኝታ እና ከምን ይሉናል ልክ ወጣ አድርጉና ፣ የትግራይ ሕዝብ ሚና ምንድን ነው የሚለውን መርምሩ ። ለኔ ቁልፉ ያለው አንድ አለመሆናችንና የትግራይ ህዝብን እንደ ሕዝብ አጋር አድርጎ መመልከቱ ላይ ይመስለኛል ። እደግመዋለሁ ፣ የትግራይ ሕዝብ ሚሊዮን ኦሮሞዎች ብታረዱ ፣ ሚሊዮን አማሮች ቢሞቱ ፣ አሁን ባሉበት ስብእናቸው አንዳች ስሜት የሚሰጣቸው ሰዎች አይደሉም ። የመንግስት ህብለሰረሰሮች ስለመሆናቸው 25 ዓመት እየራባቸው እንኳ ባሳዩት ትዕግስት ልንመዝናቸው እንችላለን ። ደርግ ላይ ተቆጥተው በረሃ የወረዱት የትግራይ ልጆች ፣ እና ስንቅ በድብቅ ለታጋዮች ሲቋጥሩ የነበሩ የትግራይ እናት እና አባቶች ፣ ዝም ያሉት ምንም ስለማያውቁ ነው ብትሉ ፣ ምክንያታችሁ በቁም ለመታረድ ከመፈረም የተለየ አድርጌ አላየውም ። ስለዚህ ይህ መንግስት ምን ይዞ ቆመ የሚለውን ድጋሚ ድጋሚ መርምሩት !