ባሌ ሮቤን መደወላቡ ዩንቨርስቲ ውጥረት ላይ ናቸው::የመዳወላቡ ዩንቨርስቲን ከከተማዋ የሚያገናኘው መስመር ታጥሯል::
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
በባሌ ሮቤ የፌዴራል ፖሊስ እና የአግኣዚ ጦር አባላት በከተማው ደርሰው በመፍሰስ እንዲሁም ከገጠሩ ወደ ከተማው የሚያስገቡ መንገዶችን በመዝጋት ከተማዋን ውጥረት ውስጥ ከተዋታል::የሮቤ መምህራን ኮሌጅን የሁለተኛ ደረጃ እና የመጀመሪያ ደረጃ ትምሕርት ቤቶችን ከበዋል::የመዳወላቡ ዩንቨርስቲ ከከተማው የሚያገናኘው መስመር በወታደሮችኡ ተቆርጦ የታጠረ ሲሆን ወደ ሮቤ ከተማ የሚመጡ የገጠር ነዋሪዎች ክመንገድ እንዲመለሱ ተደርጓል::
በመደወላቡ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች እና በወያኔ ሃይሎች መካከል ግጭት እንደተፈጠረ እየተነገረ ቢገም መረጃዎች እንዳይወጡ ወታደሮቹ አከባቢው በመክበብ ከፍተኛ ችግር እና ውጥረት እንደፈጠሩ የአከባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ::ከሁለት ቀ በፊት የመዳ ውላቡ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች በእራት ከተመገቡ በኋላ ተቃውሞ ያሰሙ የነበረ ቢሆንም በአከባቢው የአገዛዙ የታጠቁ ሃይሎች ስላልነበሩ ተቃውሞው በሰላም ተጀምሮ መጠናአቀቁ ይታወሳል::