ረሃብ ለምን ደፈረን? ዴሞ ቅጽ 41 ቁ 2 ጥቅምት 2008 ዓ.ም
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
የአገራችንን ስምና ዝና በማጉደፍ የታወቁት ረሃብና ጠኔ ዘንድሮም ጓዛቸውን ጠቅለው ይዘው አገራችንን እየጎበኙ ነው። ባሁኑ ወቅት 8.2 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ በረሃብ አለንጋ እየተገረፈ ሲሆን ከጥቂት ጊዜ በኋላ ይህ ቁጥር ወደ አስራ አምስት ሚሊዮን ያድጋል የሚል አስተያየት ጉዳዩን ከሚያውቁ ባለሙያዎች እየተነገረ ነው። በበርካታ አካባቢዎች የቀንድ እና የጋማ ከብቶች በብዛት አልቀዋል በተራበው ሕዝብ ላይም ተመሳሳይ እልቂት ሊደርስ ይችላል የሚለው ስጋት ከፍተኛ ነው። በተለያዩ አገሮች በተለይም በማደግ ላይ ባሉ አገሮች ድርቅ፤ የዝናም እጥረት፤ የምርት መቀነስ ወዘተ… በየጊዜው የሚከሰት ሲሆን ዜጎች በረሃብና በጠኔ ተሰቃዩ ሲባሉና በዓለም አቀፍ ደረጃ ምጽዋት ሲለምኑ ግን አይታይም። ለምን የሚለው ጥያቄ ሁሉም ላይ የሚያቃጭል ነው። በየጊዜው በአገራችን እየተከሰተ ያለው ድርቅና የዝናም እጥረት ለምን ዜጎቻችንን ለረሃብና ለእልቂት ያጋልጣል? አገራችን በኢኮኖሚ በድርብ አሃዝ አድጋለች መንጥቃለች፤ በዓለም ፈጣን የኢኮኖሚ እድገትን አሳይታለች ተብሎ ነጋ፣ ጠባ እየተለፈፈ ለምንድነው አሁንም ምጽዋት ለማኝ የሆነችው? መፍትሔውስ ምንድነው የሚሉት እና ሌሎች መሰል ጥያቄዎች በአዕምሮአችን የሚብላሉና መልስ ማግኘት የሚሹ ናቸው።
ያለመታደል ሆኖ የሀገራቸን አርሶአደር በገዛ አገሩ ላይ እንደ ዜጋ ክብሩ ተጠብቆም ሆነ መብቱ ተከብሮለት አያውቅም። በሚያመርተው የእርሻ ምርት ወገኑን በቀለብ ቀጥ አድረጎ የያዘ ከመሆኑ ሌላ የሀገሩን ሉዓላዊነትና ከብር ለማስጠበቅና ሀገሩን ከውጪ ወራሪዎች ለመከላከል አኩሪ የዜግነት ተግባራትን የፈፀመ ዛሬም እየፈፀመ ያለ የኅበረተሰብ ክፍል ነው። ይህ የአገሪቱ ዋልታና መሠረት የሆነው አኩሪ ዜጋ በተለያዩ ጊዜያት ሥልጣን በያዙ ገዥዎች እንደ ዝቅተኛ ዜጋ እየተቆጠረ፤ መብቱ እየተረገጠና ፍዳውን እየቆጠረ ኖሯል። “የባሰን አታምጣ” እያለ የተለመደ ስቃዩን ችሎ የቆየው ያሳለፈው ስቃይ አልበቃ ብሎት “ዳቦ ከሌለ ድንጋይ ብላ” ከሚሉ ደፋርና ወሮ በላ ካድሬዎች ዘመን ደርሷል። በአፄው ዘመነ መንግሥት በአርሶ አደር ላይ ይፈፀም የነበረውን ግፍ፤ መከራና ስቃይ በውል ያጤኑ፤ አርሶአደሩ ተቸገሮ፤ ተርቦና ተጠምቶ ያስተማራችው ወጣት ተማሪዎችና ምሁራን ” መሬት ላራሹ ለላብ አፍሳሹ” “ዳቦ ለተራበው” የሚለውን መፈክር የትግል አርማቸው አድርገው አገዛዙን ሲቃወሙ የነበሩት የአርሶአደሩ ችግር የጠቅላላ የሀገሪቱ ችግር መሆኑን በውል በማጤን ነበር። በሚያዚያ ወር 1964ዓ.ም ለብዙኃኑ የቆመውን ታጋይ ድርጅት -ኢሕአፓን- የወለደው ይኸው የአርሶ አደሩና ባጠቃላይም የጭቁኑ ሕዝብ ፍዳና መከራ ነበር።
ያለመታደል ሆኖ የሀገራቸን አርሶአደር በገዛ አገሩ ላይ እንደ ዜጋ ክብሩ ተጠብቆም ሆነ መብቱ ተከብሮለት አያውቅም። በሚያመርተው የእርሻ ምርት ወገኑን በቀለብ ቀጥ አድረጎ የያዘ ከመሆኑ ሌላ የሀገሩን ሉዓላዊነትና ከብር ለማስጠበቅና ሀገሩን ከውጪ ወራሪዎች ለመከላከል አኩሪ የዜግነት ተግባራትን የፈፀመ ዛሬም እየፈፀመ ያለ የኅበረተሰብ ክፍል ነው። ይህ የአገሪቱ ዋልታና መሠረት የሆነው አኩሪ ዜጋ በተለያዩ ጊዜያት ሥልጣን በያዙ ገዥዎች እንደ ዝቅተኛ ዜጋ እየተቆጠረ፤ መብቱ እየተረገጠና ፍዳውን እየቆጠረ ኖሯል። “የባሰን አታምጣ” እያለ የተለመደ ስቃዩን ችሎ የቆየው ያሳለፈው ስቃይ አልበቃ ብሎት “ዳቦ ከሌለ ድንጋይ ብላ” ከሚሉ ደፋርና ወሮ በላ ካድሬዎች ዘመን ደርሷል። በአፄው ዘመነ መንግሥት በአርሶ አደር ላይ ይፈፀም የነበረውን ግፍ፤ መከራና ስቃይ በውል ያጤኑ፤ አርሶአደሩ ተቸገሮ፤ ተርቦና ተጠምቶ ያስተማራችው ወጣት ተማሪዎችና ምሁራን ” መሬት ላራሹ ለላብ አፍሳሹ” “ዳቦ ለተራበው” የሚለውን መፈክር የትግል አርማቸው አድርገው አገዛዙን ሲቃወሙ የነበሩት የአርሶአደሩ ችግር የጠቅላላ የሀገሪቱ ችግር መሆኑን በውል በማጤን ነበር። በሚያዚያ ወር 1964ዓ.ም ለብዙኃኑ የቆመውን ታጋይ ድርጅት -ኢሕአፓን- የወለደው ይኸው የአርሶ አደሩና ባጠቃላይም የጭቁኑ ሕዝብ ፍዳና መከራ ነበር።
በወቅቱ የነበሩት ተማሪዎች እና የየካቲት 1966ቱ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ አራማጆች መሬት ላራሹ ለላብ አፍሳሹ ብለው ሕዝባዊ መፈክር ያስተጋቡለት፤ በግንባር ቀደምትነት የታገሉለትና ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈሉበት የመሬት ጥያቄ እስከዘሬ አልተመለሰም። አርሶአደሩ ዛሬም የመሬቱ ባለቤት አልሆነም። የመሬት ጥያቄ በአገራችን በአግባቡ መልስ እስካለገኘ ድረስና መሠረታዊ የሆኑት የኢትዮጵያ ሕዝብ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማኅበራዊ እና የፍትህ ጥያቄዎች በአግባቡ እስካልተፈቱ/እስካልተመለሱ ድረስ አገራችን ከመከራ፣ ከችግርና ከረሀብ ተላቃ በኢኮኖሚ፣ በልማትና በሥልጣኔ ጎዳና መራመድ የምትችል አይሆንም።
ኢትዮጵያ አገራችን የእለት ጉርስና መጠላያ የሌለው ሕዝብ የሚተራማስባት የምድር ሲኦል ሆናለች። ሁሉም የኢኮኖሚ የማኅበራዊ የአገልግሎት ዘርፎች ከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ገብተዋል። በምግብ እህል ራሰን መቻልና መሠረታዊ የሆኑ የፍጆታ እቃዎችን በአገር ውሰጥ ማምረት የሚያስችሉ ሁኔታዎች አልተፈጠሩም። ከጊዜ ወደጊዜ ተለዋዋጭ የሆነው የዋጋ ንረት የሠራተኛውን የነፍስ ወከፍ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ስለጎዳው ቁጥሩ ከፍተኛ የሆነው ሥራ አጥ የጥቂቱ አምራች ጥገኛ በመሆኑ የተነሳ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ተመጽዋች/ረሀብተኛ ለመሆን ተገደዋል። ወያኔ ከጥቂት ከበርቴዎችና ከባእዳን ባላቱጃሮች ጋር የጥቅም ተካፋይ በመሆን መሬትና የአገሪቱ የተፈጥሮ ሀብት በጥቂቶች እጅ እንዲገባ በማድረጉ የተነሳ በሀብታምና በደሀው መካከል ያለው ልዩነት በሚያስደነግጥ ደረጃ እጀግ ሰፍቶ ይገኛል።
የደርግ የእዝ ኢኮኖሚ የወደቀ ቢመሰልም መልኩና ስልቱን ለውጦ ዛሬም እንደትናቱ የአገሪቱ ዋና ዋና የኢኮኖሚ አውታሮች በወያኔ ቡድን በሞኖፖል (በወያኔ የእዝ ኢኮኖሚ) ተይዞ ይገኛል። ለአገሪቱ ኢኮኖሚ እጅግ ጠቃሚ የሆኑ የተለያዩ የማምረቻና የማከፋፈያ ድርጅቶች ወያኔ በፈጠራቸውና በሚቆጣጠራችው የግል ድርጀቶች ቁጥጥር ሥር ገብተዋል። የጥምር አሃዝ እድገት አሳየ እየተባለ በወዳጆቹ ይዘፈንለት እንጅ ወያኔ በየወቅቱ የሚቀይሳቸውና በሥራ ላይ የሚያውላቸው የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች እድገትን የሚያስገኙ ሳይሆን ኢኮኖሚውን የባሰ ችግር ውሰጥ የሚከቱ ሆነው ተገኝተዋል። የነጣና የዕለት ጉርስ የሌለው ሕዝብ ቁጥር ወደ 46 ሚሊዮን ይደርሳል። ከባድ በሆነ የድህነት አረንቁዋ ውስጥ ካሉት ኢትዮጵያዊያን መካከል ወደ ሰላሳ ስምንት ሚሊዮን የሚጠጉት በገጠሩ አካባቢ የሚኖሩ ሲሆን ቀሪዎቹ የከተማ ነዋሪዎች ናቸው። የወያኔ ባለሥልጣናት ድርቅ እንጅ ረሃብ የለም በማለት በተደጋጋሚ የሀሰት ጥሩምባቸውን ቢያጮሁም በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች በገባው ድርቅና ተያይዞ በተከሰተው ረሃብ ምክንያት በተለያዩ ቦታዎች የቀንድና የጋማ ከብቶች መሞታቸው ሲታወቅ በቅርቡ ረሃቡ የህጻናትን ህይወት እየቀሰፈ መሆኑ ተዘግቧል። እስካሁን ድረስ እስከ 8.2 ሚሊዮን የሚደርስ ሕዝብ በረሃቡ እየተጠቃ ነው የሚል ግምት የተሰጠ ሲሆን በተባበሩት መንግሥታት አዋቂዎች ዘገባ መሠረት ከሚቀጥለው ጥር ወር ጀምሮ የረሃብተኞች ቁጥር ወደ 15 ሚሊዮን ይጠጋል ተብሎ ተገምቷል። የሕዝብ ቁጥር በፍጥነት እያደገ በሄደበት ሁኔታ የምግብ አቅርቦቱ ተመጣጣኝ ካልሆነ ከድርቁ በተጨማሪ ሕዝብን ለረሃብና ለጠኔ የሚዳርግ መሆኑ ግልጽ ነው። ከመቶ ሰባ አምስት(75%) የሚሆነው የገጠሩ ነዋሪ ሕዝብ ዛሬም በንፁህ የመጠጥ ውሃ እጦት ይሰቃያል። የጤና ጉዳይ ከተነሳም አምራቹ ኃይል ለወባ፣ ለሳንባ ነቀርሳና ለሌሎች ተላላፊ በሽታዎች የተጋለጠ በመሆኑ በምርት ላይ የሚያደርሰው ችግር ቀላል አልሆነም።
ኢትዮጵያ አገራችን የእለት ጉርስና መጠላያ የሌለው ሕዝብ የሚተራማስባት የምድር ሲኦል ሆናለች። ሁሉም የኢኮኖሚ የማኅበራዊ የአገልግሎት ዘርፎች ከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ገብተዋል። በምግብ እህል ራሰን መቻልና መሠረታዊ የሆኑ የፍጆታ እቃዎችን በአገር ውሰጥ ማምረት የሚያስችሉ ሁኔታዎች አልተፈጠሩም። ከጊዜ ወደጊዜ ተለዋዋጭ የሆነው የዋጋ ንረት የሠራተኛውን የነፍስ ወከፍ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ስለጎዳው ቁጥሩ ከፍተኛ የሆነው ሥራ አጥ የጥቂቱ አምራች ጥገኛ በመሆኑ የተነሳ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ተመጽዋች/ረሀብተኛ ለመሆን ተገደዋል። ወያኔ ከጥቂት ከበርቴዎችና ከባእዳን ባላቱጃሮች ጋር የጥቅም ተካፋይ በመሆን መሬትና የአገሪቱ የተፈጥሮ ሀብት በጥቂቶች እጅ እንዲገባ በማድረጉ የተነሳ በሀብታምና በደሀው መካከል ያለው ልዩነት በሚያስደነግጥ ደረጃ እጀግ ሰፍቶ ይገኛል።
የደርግ የእዝ ኢኮኖሚ የወደቀ ቢመሰልም መልኩና ስልቱን ለውጦ ዛሬም እንደትናቱ የአገሪቱ ዋና ዋና የኢኮኖሚ አውታሮች በወያኔ ቡድን በሞኖፖል (በወያኔ የእዝ ኢኮኖሚ) ተይዞ ይገኛል። ለአገሪቱ ኢኮኖሚ እጅግ ጠቃሚ የሆኑ የተለያዩ የማምረቻና የማከፋፈያ ድርጅቶች ወያኔ በፈጠራቸውና በሚቆጣጠራችው የግል ድርጀቶች ቁጥጥር ሥር ገብተዋል። የጥምር አሃዝ እድገት አሳየ እየተባለ በወዳጆቹ ይዘፈንለት እንጅ ወያኔ በየወቅቱ የሚቀይሳቸውና በሥራ ላይ የሚያውላቸው የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች እድገትን የሚያስገኙ ሳይሆን ኢኮኖሚውን የባሰ ችግር ውሰጥ የሚከቱ ሆነው ተገኝተዋል። የነጣና የዕለት ጉርስ የሌለው ሕዝብ ቁጥር ወደ 46 ሚሊዮን ይደርሳል። ከባድ በሆነ የድህነት አረንቁዋ ውስጥ ካሉት ኢትዮጵያዊያን መካከል ወደ ሰላሳ ስምንት ሚሊዮን የሚጠጉት በገጠሩ አካባቢ የሚኖሩ ሲሆን ቀሪዎቹ የከተማ ነዋሪዎች ናቸው። የወያኔ ባለሥልጣናት ድርቅ እንጅ ረሃብ የለም በማለት በተደጋጋሚ የሀሰት ጥሩምባቸውን ቢያጮሁም በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች በገባው ድርቅና ተያይዞ በተከሰተው ረሃብ ምክንያት በተለያዩ ቦታዎች የቀንድና የጋማ ከብቶች መሞታቸው ሲታወቅ በቅርቡ ረሃቡ የህጻናትን ህይወት እየቀሰፈ መሆኑ ተዘግቧል። እስካሁን ድረስ እስከ 8.2 ሚሊዮን የሚደርስ ሕዝብ በረሃቡ እየተጠቃ ነው የሚል ግምት የተሰጠ ሲሆን በተባበሩት መንግሥታት አዋቂዎች ዘገባ መሠረት ከሚቀጥለው ጥር ወር ጀምሮ የረሃብተኞች ቁጥር ወደ 15 ሚሊዮን ይጠጋል ተብሎ ተገምቷል። የሕዝብ ቁጥር በፍጥነት እያደገ በሄደበት ሁኔታ የምግብ አቅርቦቱ ተመጣጣኝ ካልሆነ ከድርቁ በተጨማሪ ሕዝብን ለረሃብና ለጠኔ የሚዳርግ መሆኑ ግልጽ ነው። ከመቶ ሰባ አምስት(75%) የሚሆነው የገጠሩ ነዋሪ ሕዝብ ዛሬም በንፁህ የመጠጥ ውሃ እጦት ይሰቃያል። የጤና ጉዳይ ከተነሳም አምራቹ ኃይል ለወባ፣ ለሳንባ ነቀርሳና ለሌሎች ተላላፊ በሽታዎች የተጋለጠ በመሆኑ በምርት ላይ የሚያደርሰው ችግር ቀላል አልሆነም።
በአገራችን ለሚታየው መጠነ ሰፊ ድኽነትና እየተመላላሰ ለሚጎብኘን ረሀብ በዋነኛነት ተጠያቂው የመልካም አስተዳደር እጦት ነው። የኋላቀርነታችንና የድኽነታችን ምንጭ የአስተዳደር ድከመት፤ የአመራር ጉድለትና የፍትህ መዛባት መፈራረቃቸው ለመሆኑ የአደባባይ ምስጢር ከሆነ ዘመናትን አስቆጥሯል። እነሆ ዛሬም ቢሆን ታታሪና ጠንካራ ሠራተኛ የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ የድካሙን ፍሬ መጠቀምና መቋደስ ያልቻለው ከጎኑ የሚቆም፣ የሚረዳው፣ አይዞህ የሚለውና የሚያስተባበረው መሪ ባለማግኘቱ ነው።
ወያኔ ከፍጥረቱ ጀምሮ በየጊዜው በሚፈፅማቸው ፀረ-ሕዝብና ጸረ-አገር ተግባራት የሕዝብ አመኔታን ያላገኘና ከሕዝብ የተነጠለ መሆኑ ግልጽ ነው። በሕዝብ ላይ ያለው የበቀል ስሜትና ጥርጣሬ ከፍተኛ በመሆኑ ሕዝብ በፖለቲካው ብቻ ሳይሆን በልማት አጀንዳዎች ላይ በነፃነት እንዳይመክርና እንዳይሳተፍ አድርጓል።
አገዛዙ በየጊዜው የሚያወጣችው የኢኮኖሚ መመሪያዎችና ፖሊሲዎች እንዲሁም እነዚህኑ ተግባራዊ ለማድረግ የሚወስዳቸው እርምጃዎች የሚያረጋግጡት ይህንኑ እውነታ እንጂ፣ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ያላቸውን ንዋይ በኢንዱስቲሪና ልማት ዘርፍ እንዲያውሉ የሚያበረታታ አይደለም። የወያኔ አገዛዝ ከታሪክና ከስህተት ለመማርና ተምሮም ለመስተካከል ባህርዩና ተፈጥሮው የማይፈቅድሉት በመሆኑ በየጊዜው ለሚከሰቱ እንደ ድርቅና ረሃብ ለመሳሰሉት ችግሮች ዘላቂ የሆነ መፈትኄ ከመስጠት ይልቅ ተፈጥሮንና ለጋሽ አገሮችን ሲኮንና ሲያወግዝ ይደመጣል።
በዓለማችንም ሆነ በሀገራቸን የድርቅ ክስተት የረጅም ጊዜ ታሪክ ያለው የተፈጥሮ ባሕርይ ነው። ድርቅ ጥንትም ሲከሰት የነበር ዛሬም ሆነ ወደፊትም ሊከሰት የሚችል የአየር ለውጥ ነው። ለድርቅ መንስኤ ናቸው ተብለው ከሚጠቀሱ ምክንያቶች ውስጥ፡- የሕዝብ ቁጥር መጨመር፤ ለእርሻ ተግባር የሚውለው መሬት ለምነት መቀነስ፤ ከኋላ ቀር የአስተራረስ ዘዴ የተነሳ ከእርሻው ክፈለ-ኤኮኖሚ የሚገኘው የምርት ውጤት ሕዝቡን መመገብ አለመቻል- የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ሲሆኑ፤ በአንድ ሀገር ውስጥ ለሚከሰት ረሀብ ግን ምክንያቱ በሥልጣን ላይ ያለው አገዛዝ የሚከተለው የተሳሳተ የኢኮኖሚና የልማት ፖሊሲ መሆኑ ጥርጥር የለውም።
ወያኔ ከፍጥረቱ ጀምሮ በየጊዜው በሚፈፅማቸው ፀረ-ሕዝብና ጸረ-አገር ተግባራት የሕዝብ አመኔታን ያላገኘና ከሕዝብ የተነጠለ መሆኑ ግልጽ ነው። በሕዝብ ላይ ያለው የበቀል ስሜትና ጥርጣሬ ከፍተኛ በመሆኑ ሕዝብ በፖለቲካው ብቻ ሳይሆን በልማት አጀንዳዎች ላይ በነፃነት እንዳይመክርና እንዳይሳተፍ አድርጓል።
አገዛዙ በየጊዜው የሚያወጣችው የኢኮኖሚ መመሪያዎችና ፖሊሲዎች እንዲሁም እነዚህኑ ተግባራዊ ለማድረግ የሚወስዳቸው እርምጃዎች የሚያረጋግጡት ይህንኑ እውነታ እንጂ፣ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ያላቸውን ንዋይ በኢንዱስቲሪና ልማት ዘርፍ እንዲያውሉ የሚያበረታታ አይደለም። የወያኔ አገዛዝ ከታሪክና ከስህተት ለመማርና ተምሮም ለመስተካከል ባህርዩና ተፈጥሮው የማይፈቅድሉት በመሆኑ በየጊዜው ለሚከሰቱ እንደ ድርቅና ረሃብ ለመሳሰሉት ችግሮች ዘላቂ የሆነ መፈትኄ ከመስጠት ይልቅ ተፈጥሮንና ለጋሽ አገሮችን ሲኮንና ሲያወግዝ ይደመጣል።
በዓለማችንም ሆነ በሀገራቸን የድርቅ ክስተት የረጅም ጊዜ ታሪክ ያለው የተፈጥሮ ባሕርይ ነው። ድርቅ ጥንትም ሲከሰት የነበር ዛሬም ሆነ ወደፊትም ሊከሰት የሚችል የአየር ለውጥ ነው። ለድርቅ መንስኤ ናቸው ተብለው ከሚጠቀሱ ምክንያቶች ውስጥ፡- የሕዝብ ቁጥር መጨመር፤ ለእርሻ ተግባር የሚውለው መሬት ለምነት መቀነስ፤ ከኋላ ቀር የአስተራረስ ዘዴ የተነሳ ከእርሻው ክፈለ-ኤኮኖሚ የሚገኘው የምርት ውጤት ሕዝቡን መመገብ አለመቻል- የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ሲሆኑ፤ በአንድ ሀገር ውስጥ ለሚከሰት ረሀብ ግን ምክንያቱ በሥልጣን ላይ ያለው አገዛዝ የሚከተለው የተሳሳተ የኢኮኖሚና የልማት ፖሊሲ መሆኑ ጥርጥር የለውም።
ወያኔ መሬትን በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ያደረገው በዘር ላይ የተመሠረተ የፖለቲካ ፖሊሲውን ለማራመድና ሕዝቡን በመያዣነት ለማፈንና ለመቆጣጠር ነው። በዚህ ጨቋኝ ፖሊሲ የተነሳ ግን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ለረሐብና ለበሽታ ተጋልጠዋል። መሬት በአገዛዙ ቁጥጥር ሥር በመዋሉ ታታሪውና አምራቹ አርሶ አደር በትጋት ወደልማቱ እንዳያተኩር ትልቅ ጋሬጣ ደቅኖበታል። ዛሬ በወያኔ ብልሹ ፖሊሲ ምክንያት የብር ዋጋ እጅግ በመቀነሱ ለዘመናዊ እርሻም ሆነ ለፋብሪካ የሚሆኑ መሳሪያዎችንና ጥሬ እቃዎችን ከውጪ ለማስመጣት ለሚጥሩ ሀገር በቀል ባለሃብቶች የውጭ ምንዛሪን ማግኘት የሰማይን ያህል ርቆባቸዋል። የሀገር ውስጥ ባለሀበት ከባንክ ተበድሮ የልማት ሥራ እንዳያካሂድ ወለዱ ንሮበታል። በአንጻሩ የወያኔ ባለሥልጣናት የአገሪቱ አንጡራ ሀብት የሆነውን ለም የእርሻ መሬት ሕዝቡን እያፈናቀሉና እያባረሩ ለውጪ ባላሀብቶች በርካሽ በመቸብቸብ ከፍተኛ ገንዘብ በመዝረፍ ላይ ይገኛሉ።
በአገር ውስጥ ባንኮች በአነስተኛ ወለድና ከቀረጥ ነጻ የሆነ ኢንዱስትሪን ማስፋፋት በሚል ፌዝ የቻይና፣ የቱሪክ፣ የሕንድ፣ የፓኪስታንና የአረብ፣ … ወዘተ ቱጃሮች በቀላሉ አገሪቱን እንዲቀራመቱ በሩን ከፍቶላቸዋል። ወያኔ በዚህ ብቻ ሳይገታ አገራችን ካላት አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሃያ ሰባት ሺህ ሁለት መቶ (1,127,200) እስክዌር ኪሎ ሜትር የቆዳ ሥፋት መሬት ውስጥ ሥድሳ-አራት (64,000) ሺህ እስኩዌር ኪሎሜትር (6%) የሚሆነውን መሬታችንን ለሱዳን አሳልፎ ሰጥቷል። ይህ ለባዕድ የተሰጠው መሬት ቢያንስ ከሁለት መቶ (200) ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ የግዛት ቁጥጥር ስር የቆይ ለመሆኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተመሰከረ ነው።
በርካታ የዓለም አቀፍ የምርምር ተቋማትና ጥናቶች እንዳረጋገጡት ከሆነ አገራችን በከርሰ ምድሯ በሚገኝ ሀብትም ሆነ ከምድር በላይ ባላት የተፈጥሮ ሀብት የበለፅገችና በቂ ክምችት ያላት አገር ናት። ያለመታደል ሆኖ ግን በዓለም ላይ ስሟ የሚጠራው በድኽነትና በረሀብ ነው።
በመሠረቱ ድርቅ ብቻውን ለረሀብ አይዳርግም። ድርቅ ረሀብን የሚወልደው የኅብረተሰቡ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መሠረት ደካማ ሲሆን ብቻ ነው። ጠንካራ የኢኮኖሚ መሠረት ያላቸው፣ በማኅበራዊ ተቋምና አገልግሎት በሚገባ የተደራጁ አገሮች ድርቅን ሳይሆን የድርቅን ተጽእኖ መቋቋም ችለዋል። በድኽነት ላይ የተመሠረተ ኑሮና ከእጅ ወደ አፍ የማምረት ዘይቤ በአንድ ወቅት የሚደርስ የሰብል መበላሸትን ወይም መቀነስን ሊቋቋም የማይችል መሆኑ ግልጽ ነው። አንድ የድርቅ ወቅት ሕዝቡን በስደት ለመፈናቀልና ለእልቂት ይዳርገዋል። በአንጻሩ ጠንካራ የኢኮኖሚ መሠረት ያለው፤ ከእጅ ወደአፍ ከሆነ አምራችነት የተላቀቀ፤ ከዓመት ልብስና ከእለት ጉርስ በብዙ እጅ የበለጠ ምርት የሚያመርት ሕዝብና ለክፉ ቀን የሚሆነውን ጥሪት ያዳበረ ኅብረተስብ በአንድ ወይም በሁለት ዓመታት በሚከሰት ድርቅ ለረሃብና ለሞት አይዳረግም። በመሆኑም የረሀብ መሠረታዊ ምክንያት ድርቅ ሳይሆን ድኽነትና ኋላቀርነት ነው። የድኽነትና የኋላቀርነት ዋና መንስኤ ደግሞ የዴሞክራሲና የመብት አለመረጋገጥ እንዲሁም የመልካም አስተዳደር፣ የፍትህ እጦት ነው ።
በርካታ የዓለም አቀፍ የምርምር ተቋማትና ጥናቶች እንዳረጋገጡት ከሆነ አገራችን በከርሰ ምድሯ በሚገኝ ሀብትም ሆነ ከምድር በላይ ባላት የተፈጥሮ ሀብት የበለፅገችና በቂ ክምችት ያላት አገር ናት። ያለመታደል ሆኖ ግን በዓለም ላይ ስሟ የሚጠራው በድኽነትና በረሀብ ነው።
በመሠረቱ ድርቅ ብቻውን ለረሀብ አይዳርግም። ድርቅ ረሀብን የሚወልደው የኅብረተሰቡ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መሠረት ደካማ ሲሆን ብቻ ነው። ጠንካራ የኢኮኖሚ መሠረት ያላቸው፣ በማኅበራዊ ተቋምና አገልግሎት በሚገባ የተደራጁ አገሮች ድርቅን ሳይሆን የድርቅን ተጽእኖ መቋቋም ችለዋል። በድኽነት ላይ የተመሠረተ ኑሮና ከእጅ ወደ አፍ የማምረት ዘይቤ በአንድ ወቅት የሚደርስ የሰብል መበላሸትን ወይም መቀነስን ሊቋቋም የማይችል መሆኑ ግልጽ ነው። አንድ የድርቅ ወቅት ሕዝቡን በስደት ለመፈናቀልና ለእልቂት ይዳርገዋል። በአንጻሩ ጠንካራ የኢኮኖሚ መሠረት ያለው፤ ከእጅ ወደአፍ ከሆነ አምራችነት የተላቀቀ፤ ከዓመት ልብስና ከእለት ጉርስ በብዙ እጅ የበለጠ ምርት የሚያመርት ሕዝብና ለክፉ ቀን የሚሆነውን ጥሪት ያዳበረ ኅብረተስብ በአንድ ወይም በሁለት ዓመታት በሚከሰት ድርቅ ለረሃብና ለሞት አይዳረግም። በመሆኑም የረሀብ መሠረታዊ ምክንያት ድርቅ ሳይሆን ድኽነትና ኋላቀርነት ነው። የድኽነትና የኋላቀርነት ዋና መንስኤ ደግሞ የዴሞክራሲና የመብት አለመረጋገጥ እንዲሁም የመልካም አስተዳደር፣ የፍትህ እጦት ነው ።
ዛሬ በአገራችን በያመቱ በረሃብ አለንጋ የሚጠበሰውና የሚሰቃየው ወገናችን የመሥራት ችግር ኖሮት ወይም ችግርን የመቋቋም ችሎታ አንሶት አይደለም። የኢትዮጵያ ሕዝብ እጅግ ታታሪና የፈጠራ ችሎታም ያለው ሕዝብ ነው። የሀገሪቱ መልከዓ ምድራዊ አቀማመጥ አስቸጋሪ በሆነበት ተራራማና ገደለማ ቦታዎች እንኳን ሳይቀር ወገቡን በገመድ ጠፍሮ ከገደል ላይ ተንጠልጥሎ፤ ቆፍሮ ለማምረት የሚጥርና የሚለፋ በራሱ የሚተማመን ኩሩ ሕዝብ ነው። ለም አፈሩ በጎርፍ ተጠርጎበት ማምረት ሲያቅተው ከዳገት የወረደውን ደለል አጠራቅሞ አፈሩን በማልማት ለማምረት የሚችል ትጉ ሕዝብ ነው። ሰብሉ በዱር አራዊትና በአእዋፍ አንዳይበላበት ማማ ሰርቶ ሲከላከል የሚውል፤ ዝናብና ቁር ሳያግደው ሲንከራተት በወባና በተስቦ በሽታ እየተሰቃየ ግን በደካማ ጉልበቱ እንኳ አርሶ ለመብላት የሚጥር ታታሪ ሕዝብ ነው።
ሕዝባችን ለረሃብ የተዳረገው የሀገሪቱ የተፈጥሮ ሃብት ደሀ ሆኖም አይደለም፡፡ ለእርሻ አመቺ ከሆነው አሥራ ስደሰት (16) ሚሊዮን ሔከታር መሬት ውስጥ ሥራ ላይ የዋለው በጣም ጥቂቱ ነው። ታታሪና አምራች ሕዝብ እያለን፤ ሥራ ላይ ያልዋለ የሀብት ምንጭ ሞልቶ ለምን ተራብን? ብሎ መጠየቅ አግባብነት ያለው ጥያቄ ነው። መልሱም ግልፅና አጭር ነው። የአገራችን አርሶ አደር የሚያግዘው ሳይሆን የሚጫነው፤ የሚሰጠው ሳይሆን የሚነጥቀው ስለበዛበት ነው። አማራቹ ኃይል የተረጋጋ ህይወት ኖሮት ኑሮን ለማሻሻልና ቤተሰቡን በሚገባ መግቦ ለማሳዳር ለአንዴም ፋታ ያገኘበት ወቅት አለ ለማለት ያስቸግራል። በገዥዎቹ የሚወጡት የኢኮኖሚ/የእርሻ ፖሊሲዎች በሙሉ ራስ መቻልን፤ በራስ መተማመንና ምርታማነትን የሚያበረታቱ አልነበሩም አሁንም አይደሉም።
የሚቀየሱት የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች ሁሉ የሕዝቡን የአደጋ መከለከያ ስልቶች የሚያዳክሙ ምርትንና ምርታማነትን የሚያግቱ ከመሆናቸውም አልፎ ሕዝብ በመንግሥት ላይ፤ መንግሥት በሕዝብ ላይ እምነት እንዳይኖረው ስለተደረገ፤ ሕዝቡ ለድኽነትና ለችግር ተጋልጧል። በድርቅ ተፅእኖ በቀላሉ የማይደፈረው አካባቢ ዛሬ በአነሰተኛ የሰብል መጥፋት የተነሳ ሕዝቡ ለከፋ ረሀብ ተዳርጓል። ለክፉ ቀን ብሎ እህል በጉድጓድ ያስቀምጥ የነበረውና፤ ለዘር ይሆነኛል ብሎ ያስቀመጠውን እህል መብላት እንደ “እርም” ይቆጥር የነበረው አርሶ አደር በአገዛዙ የኢኮኖሚ ፖሊሲ የተነሳ ዛሬ ጥሪት እንኳ እንዳይኖረው ተደርጓል።
አረሶ አደር ሆኖ የኔ ነው የሚለው የግል ማሳ፤ ገበሬ ሆኖ ለማረስ የሚያስችለው ጥማድ በሬ የለውም። አርሶ አደሩ ዛሬ የአገዛዙ ጭሰኛ ሆኗል። እነዚህና ከሌሎች የተሳሳቱ የአገዛዙ የፖሊቲካ፣ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ፖሊሲዎች ጋር ተዳምረው የኢትዮጵያን ብሔራዊ ኢኮኖሚ መቅኖ ከማሳጣታቸውም በላይ ሕዝቡን ለስደት፣ ለረሀብና ለበሽታ ዳርገውታል።
ወያኔ በሕዝባችን ላይ ግፍና ደባ እየፈጸመ ያለው በነፃ ኢኮኖሚ መርህ ስም ነው። በነፃ የገበያ ኢኮኖሚ ስም የሀገሪቱ ሀብት ጎሳዊ ለሆነ አድሎአዊ ጥቅም ውሏል። ወያኔ ሀብትን ወደግል ይዞታ ማዛወር በሚል
የሚቀየሱት የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች ሁሉ የሕዝቡን የአደጋ መከለከያ ስልቶች የሚያዳክሙ ምርትንና ምርታማነትን የሚያግቱ ከመሆናቸውም አልፎ ሕዝብ በመንግሥት ላይ፤ መንግሥት በሕዝብ ላይ እምነት እንዳይኖረው ስለተደረገ፤ ሕዝቡ ለድኽነትና ለችግር ተጋልጧል። በድርቅ ተፅእኖ በቀላሉ የማይደፈረው አካባቢ ዛሬ በአነሰተኛ የሰብል መጥፋት የተነሳ ሕዝቡ ለከፋ ረሀብ ተዳርጓል። ለክፉ ቀን ብሎ እህል በጉድጓድ ያስቀምጥ የነበረውና፤ ለዘር ይሆነኛል ብሎ ያስቀመጠውን እህል መብላት እንደ “እርም” ይቆጥር የነበረው አርሶ አደር በአገዛዙ የኢኮኖሚ ፖሊሲ የተነሳ ዛሬ ጥሪት እንኳ እንዳይኖረው ተደርጓል።
አረሶ አደር ሆኖ የኔ ነው የሚለው የግል ማሳ፤ ገበሬ ሆኖ ለማረስ የሚያስችለው ጥማድ በሬ የለውም። አርሶ አደሩ ዛሬ የአገዛዙ ጭሰኛ ሆኗል። እነዚህና ከሌሎች የተሳሳቱ የአገዛዙ የፖሊቲካ፣ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ፖሊሲዎች ጋር ተዳምረው የኢትዮጵያን ብሔራዊ ኢኮኖሚ መቅኖ ከማሳጣታቸውም በላይ ሕዝቡን ለስደት፣ ለረሀብና ለበሽታ ዳርገውታል።
ወያኔ በሕዝባችን ላይ ግፍና ደባ እየፈጸመ ያለው በነፃ ኢኮኖሚ መርህ ስም ነው። በነፃ የገበያ ኢኮኖሚ ስም የሀገሪቱ ሀብት ጎሳዊ ለሆነ አድሎአዊ ጥቅም ውሏል። ወያኔ ሀብትን ወደግል ይዞታ ማዛወር በሚል
ሰበብ ከውርስ ባልተለየ ሁኔታ የሕዝብን ሀብትና ንብረት በምርጥ አባላቱና በዙሪያው በኮለኮላቸው ተለጣፊ ድርጅቶች አባሎችና ቤተሰቦቻቸው ስም በእጁ አሰገብቶአል።
በልማቱ መስክ ለራሱና ለሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ ቁልፍ ሚና ሊጫወት የሚችለው የተማረና በሥራ ልምድ ተመክሮን ያካበተው የሰው ኃይል ከሥራው እየተባረረና እየተሰደደ በመስኩ እውቀትና ልምድ በሌላቸው የአገዛዙ ካድሬዎች እንዲተኩ ተደርገዋል።
ወያኔ በሚከተለው የጎሳ ፖለቲካ (የአፓርታይድ ፖሊሲ) የተነሳ የሀገሪቱ ዜጎች በሙያቸው፤ በጉልበታቸውና በገንዘባቸው በሀገራችን የተለያዩ ክፍሎች እንዳይዘዋወሩና በፈቀዱት የሥራ መስክና አካባቢ እንዳይሰሩ ማነቆ በመሆኑ ለሥራ አጥነትና ለረሀብ ተዳርገዋል። አገዛዙ ከተወሰነ ክልል ውጭ ባሉ የሀገሪቱ ክፍሎች የልማት ሥራዎች እንዳይሰሩም ሆነ መዋዕለ ነዋይ እንዳይፈስ የማይሽርበው ሴራ የለም። በሌላ በኩል ደግሞ ለመዋዕለ ንዋይ አቅርቦት እየተባለ የተለያዩ ጥቅሞችን በስውር ዘዴ በማግኘት የወያኔ ባለሥልጣናት በብድር ስም በገፍ ወደ አገር ውስጥ የሚያስገቡት ገንዘብ አገሪቱን ከፍተኛ እዳ ውስጥ ዘፍቋታል።
የከተማንም ሆነ የገጠር መሬትን በባላቤትነት በሞኖፖል በመያዝ ሕዝቡ የአገዛዙ ጭሰኛ እንዲሆን ከማደረጉም በላይ በሊዝ ፖሊሲ ስም የሀገሪቱ አንጡራ ሀብት የሆነውን መሬት ለባዕዳን አሳልፎ በመሸጡ ኢትዮጵያዊው ዜጋ በአገሩ የበይ ተመልካች እንዲሆን ተገዷል። ይህ አጥፊ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ሆን ተብሎ ሀገሪቷንና ሕዝቡዋን በመግደል ወያኔን በሥልጣን ላይ ለማቆየት እና የቡድንና የጎሳ ፍላጎትን ለማሟላት በረዥሙ ታቅዶ የተዘጋጀ ሲሆን በዚህ ፖሊሲም ተጠቃሚዎቹ ወያኔና ባዕዳን ኃይላት መሆናቸው በገሃድ የሚታይ ነው።
የወያኔ አገዛዝ ለባእዳን ጥቅም ያደረ ከመሆኑም በላይ በየጊዜው ከባእዳኑ ጋር ከሕዝብ ጀርባ በሚያደርጋቸው ውሎችና ስምምነቶች የተነሳ በሕዝብ ላይ የሚደርሰው ችግርና መከራ ተባብሶ ይገኛል። የአገራችን የተፈጥሮ ሀብት የሆኑት ብርቅዬ የዱር እንስሳት፣ የተፈጥሮ ደኖችና የውሃ ሀብቶቻችን ለከፍተኛ አደጋ ተጋልጠዋል። በዚህም የተነሳ ለዘለቄታው በአገራችን የአየር ንብረት ላይ ሊከተል የሚችለውን አሉታዊ ሰጋት በመስኩ የተሰማሩ ባለሙያ የሆኑ ምሁራን የሚያወጡዋቸው ጥናቶች ያመለክታሉ።
ሀገራችን ኢትዮጵያ በዓለም ከመጨረሻዎቹ ተርታ ድኻ ተብለው ከተመደቡት አገሮች መካከል አንዱዋ ናት። ሰማንያ ከመቶ (80%) የሚሆነው ሕዝብ የሚተዳደረው በእርሻው ኢኮኖሚ ዘርፍ ሲሆን መሬት በመንግሥት ስም በወያኔ አገዛዝ ቁጥጥር ስር ስለሆነና አርሶ አደሩ መሬቱን የኔ ነው ብሎ እንደ ልጁ ተንከባክቦ እየጠበቀ ምርታማንቱን ለማሳዳግ ባለመቻሉ የእርሻው ክፍለ ኢኮኖሚ የአምራቹን አረሶ አደርም ሆነ የከተማውን ነዋሪ የምግብ ፍጆታ የሚያሟላ ሆኖ አልተገኘም። ስለሆነም ዋና ችግር አርሶ አደሩ በሚያርሰው መሬት ላይ የይዞታ መብት ብቻ ሳይሆን የባለቤትነት መብት ማለትም መሬቱን የመሸጥ፣ የመለወጥ፣ የማውረስ፣ በዋስትና የማስያዝ፣ …ወዘተ መብቱን ማወቅና በሕግ ማረጋገጥ ባለመቻሉና የአገዛዙ/የወያኔ ጭሰኛ በመሆኑ እንደሆነ ሊሰመርበት ይገባል።
ወያኔ በሚከተለው የጎሳ ፖለቲካ (የአፓርታይድ ፖሊሲ) የተነሳ የሀገሪቱ ዜጎች በሙያቸው፤ በጉልበታቸውና በገንዘባቸው በሀገራችን የተለያዩ ክፍሎች እንዳይዘዋወሩና በፈቀዱት የሥራ መስክና አካባቢ እንዳይሰሩ ማነቆ በመሆኑ ለሥራ አጥነትና ለረሀብ ተዳርገዋል። አገዛዙ ከተወሰነ ክልል ውጭ ባሉ የሀገሪቱ ክፍሎች የልማት ሥራዎች እንዳይሰሩም ሆነ መዋዕለ ነዋይ እንዳይፈስ የማይሽርበው ሴራ የለም። በሌላ በኩል ደግሞ ለመዋዕለ ንዋይ አቅርቦት እየተባለ የተለያዩ ጥቅሞችን በስውር ዘዴ በማግኘት የወያኔ ባለሥልጣናት በብድር ስም በገፍ ወደ አገር ውስጥ የሚያስገቡት ገንዘብ አገሪቱን ከፍተኛ እዳ ውስጥ ዘፍቋታል።
የከተማንም ሆነ የገጠር መሬትን በባላቤትነት በሞኖፖል በመያዝ ሕዝቡ የአገዛዙ ጭሰኛ እንዲሆን ከማደረጉም በላይ በሊዝ ፖሊሲ ስም የሀገሪቱ አንጡራ ሀብት የሆነውን መሬት ለባዕዳን አሳልፎ በመሸጡ ኢትዮጵያዊው ዜጋ በአገሩ የበይ ተመልካች እንዲሆን ተገዷል። ይህ አጥፊ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ሆን ተብሎ ሀገሪቷንና ሕዝቡዋን በመግደል ወያኔን በሥልጣን ላይ ለማቆየት እና የቡድንና የጎሳ ፍላጎትን ለማሟላት በረዥሙ ታቅዶ የተዘጋጀ ሲሆን በዚህ ፖሊሲም ተጠቃሚዎቹ ወያኔና ባዕዳን ኃይላት መሆናቸው በገሃድ የሚታይ ነው።
የወያኔ አገዛዝ ለባእዳን ጥቅም ያደረ ከመሆኑም በላይ በየጊዜው ከባእዳኑ ጋር ከሕዝብ ጀርባ በሚያደርጋቸው ውሎችና ስምምነቶች የተነሳ በሕዝብ ላይ የሚደርሰው ችግርና መከራ ተባብሶ ይገኛል። የአገራችን የተፈጥሮ ሀብት የሆኑት ብርቅዬ የዱር እንስሳት፣ የተፈጥሮ ደኖችና የውሃ ሀብቶቻችን ለከፍተኛ አደጋ ተጋልጠዋል። በዚህም የተነሳ ለዘለቄታው በአገራችን የአየር ንብረት ላይ ሊከተል የሚችለውን አሉታዊ ሰጋት በመስኩ የተሰማሩ ባለሙያ የሆኑ ምሁራን የሚያወጡዋቸው ጥናቶች ያመለክታሉ።
ሀገራችን ኢትዮጵያ በዓለም ከመጨረሻዎቹ ተርታ ድኻ ተብለው ከተመደቡት አገሮች መካከል አንዱዋ ናት። ሰማንያ ከመቶ (80%) የሚሆነው ሕዝብ የሚተዳደረው በእርሻው ኢኮኖሚ ዘርፍ ሲሆን መሬት በመንግሥት ስም በወያኔ አገዛዝ ቁጥጥር ስር ስለሆነና አርሶ አደሩ መሬቱን የኔ ነው ብሎ እንደ ልጁ ተንከባክቦ እየጠበቀ ምርታማንቱን ለማሳዳግ ባለመቻሉ የእርሻው ክፍለ ኢኮኖሚ የአምራቹን አረሶ አደርም ሆነ የከተማውን ነዋሪ የምግብ ፍጆታ የሚያሟላ ሆኖ አልተገኘም። ስለሆነም ዋና ችግር አርሶ አደሩ በሚያርሰው መሬት ላይ የይዞታ መብት ብቻ ሳይሆን የባለቤትነት መብት ማለትም መሬቱን የመሸጥ፣ የመለወጥ፣ የማውረስ፣ በዋስትና የማስያዝ፣ …ወዘተ መብቱን ማወቅና በሕግ ማረጋገጥ ባለመቻሉና የአገዛዙ/የወያኔ ጭሰኛ በመሆኑ እንደሆነ ሊሰመርበት ይገባል።
ከዚህ አዙሪት መውጣት የሚቻለውና የአገሪቷን የልማት እርምጃ አፋጥኖ ሕዝቡን ከድኽነትና ከረሃብ ማላቀቅ የሚቻለው በቅድሚያ በሀገሪቱ የሕዝብን መብት የጠበቀና ሕዝብን ያሳተፈ ዴሞክራሲያዊ የፖሊቲካ ሥርዓት እውን ሲሆንና የሀገርንና የሕዝብን ብሔራዊ ጥቅም ያስቀደመ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ተነድፎ ተግባራዊ ሲሆን ነው ብሎ ኢሕአፓ ያምናል። የሕዝብ መሠረታዊ ነፃነትና መብት መከበርና የኢኮኖሚ እድገት ተነጣጥለው የሚታዩ አይደሉም፤- ሁለቱ ተደጋጋፊዎች እንጅ ተፃፃራሪዎች አይሆኑም። በነፃ የመንቀሳቀስ፤ የማሰብና ሃሳብን ወደ ተግባር የመቀየር ነፃ መብት ከሌለ የራስ አነሳሽነትንና አፋልቂነትን መሠረት ያደረገ የልማት እንቅስቃሴ ከቶ የሚቻል አይሆንም። ወያኔ በዘር ላይ የተመሠረተ የክልል አገዛዝን አዋቅሮ ባለበት ሁኔታ በጋራ ወይም በኅብረት ላይ የተመሠረተ ብሔራዊ/አገራዊ እድገትና ብልፅግና ከቶ ሊመጣ የማይችል መሆኑን ኢሕአፓ ደጋግሞ ገልጿል።
ስለሆነም ድርቅን እንቆጣጠራለን የሚል ቅዠት ባይኖረንም በድርቅ ሳቢያ እየገባ በየጊዜው ወገኖቻችንን የሚጨርሰውን ረሃብ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማጥፋት የወያኔን አፋኝ ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ በተባበረ ክንድ እናስወግድ እንላለን።
ረሃብ ከአገራችን ይጠፋል !
ሕዝብ በተባበረ ትግል መብቱን ያስከብራል !
ስለሆነም ድርቅን እንቆጣጠራለን የሚል ቅዠት ባይኖረንም በድርቅ ሳቢያ እየገባ በየጊዜው ወገኖቻችንን የሚጨርሰውን ረሃብ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማጥፋት የወያኔን አፋኝ ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ በተባበረ ክንድ እናስወግድ እንላለን።
ረሃብ ከአገራችን ይጠፋል !
ሕዝብ በተባበረ ትግል መብቱን ያስከብራል !