የፓሪስ ጥቃት ፈጻሚዎች አንዱ ታወቀ::የአንዱ ቤተሰቦች ተይዘዋል::የተጠቀሙበት መኪናም ተገኝቷል::


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


#Parisattacks : የፓሪስ ጥቃት ፈጻሚዎች አንዱ ታወቀ::የአንዱ ቤተሰቦች ተይዘዋል::የተጠቀሙበት መኪናም ተገኝቷል::

የፈረንሳይ ባለስልጣናት እንዳሉት በፓሪስ ግድያ ከፈጸሙት አንዱ የሆነውና መሳሪያ ታጥቆ ጥቃት ሲያደር ነበር ያለውን ግለሰብ ማንነቱን ማወቁን ይፋ አድርገዋል
::በወቅቱ በሙዚቃ ድግሱ አከባቢ የነበሩትን ምርመራዎች ተከታትሎ ደረስኩበት ያለው ግለሰብ ሶሪያዊው የ29 አመቱ ኦመር መህመድ ነው::የተጠቀመበት መኪናም በቁጥጥር ስር ውላለች::

ይህ 89 ሰዎች ከተገደሉበት ቦታ ላይ ሲንቀሳቀስ የነበረው ግለሰብ ሽብሩን ካቀናበሩት እና ከፈጸሙት አሸባሪዎች አንዱ መሆኑን ጉዳዩን የሚከታተሉት አቃቢ ሕግ ይናገራሉ::ከዚሁ ጋር በተያያዘ ጥቃቱን ከፈጸሙን አንዱ ቤተሰቦቹ በፖሊስ እጅ መግባታቸው ሲታወቅ አስፈላጊው ምርመራ ተጀምሮባቸዋል::በፓሪስ ከተማዋ ዳርቻ የሚኖሩት ፈረንሳይ ውስጥ የተወለዱ እንደሆነ ቢነገርም ማንነታቸው አልታወቀም::ለጊዜው ምርመራ ላይ ስለሆኑ ዝርዝር ጉዳዩን ለመናገር ፖሊስ ፈቃደኛ አልሆነም::የቤልጄም ፖሊሶችን ከዚሁ ጥቃት ጋር ተያያዥነት አላቸው ያሏቸውን ሰዎች ሁሉ ሰብስበው በማሰር ልይ ይገኛሉ::

ሙሉ ዝርዝሩን እዚህ ላይ ያንብቡ::

 

First Paris Attacks gunmen identified, car used in attacks found