ጥፋተኞችም እኛ … መፍትሄዎችም እኛው …..የለውጥ ሃይሎች ነን የምንል ቆም ብለን ልናስብ ይገባል::
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
Minilik Salsawi – መቸም ራስን ማወቅ ራስን ማግኘት የመሰለ ነገር የለም::ይህ እውቀት አዘል ለሆነ ለበሰለ ሰው ይገባዋል:: ስሜትና ፕሮፓጋንዳ ለተደበላለቁበት ጫፍ አንባቢ ዘራፍ ባይ ደግሞ ላይዋጥለት ይችላል::የለውጥ ሃይል ነን የምንል ከሆነ ቆም ብለን ራሳችንን ልንዳብስ ይገባል ልንፈትሽም ይገባል:: ሃገር እየፈረሰ ወገን እየታሰረ እየሰደደ እየተንገላታ ከዚህም አልፎ እየተገደለ ነው:: በየማህበራዊ ድህረገጹ የሚወራው ሆይሆይታ እና መሬት ላይ ያለው ጉዳይ ደሞ አይገናኝም::እውነተኛ የትግል መንፈስ ይዞ ትክክለኛውን ግብ ለመምታት መፍትሄ መሆንን የመሰለ ነገር የለም:: መፍትሄው ደሞ እኛ ራሳችን ነን::ስለ ዘረኝነት ስለ ጀግንነት ስለ ልማት ስለ አዋቂነት ስለ ጡዘት ስላሌለ ነገር ወዘተ እየተሰበክን ነው:: እኛም ከየወገን ወገኑ ሆነን እየተቧደንን በየአጀንዳው ውሮሸባውን እያቀለጥነው ነው::
ከአመት አመት የምንናገረው ነገር አለ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለውጥ ይፈልጋል::የፖለቲካ ጫና ከጫንቃው ላይ እንደወርድ ይሻል::የኑሮ ውድነት ወገቡን ቆርጦታል::የማህበረሰቡ መዘበራረቅ ራስ ምታት ሆኖበታል ከዚህ ጋር በተመሳሰሉ ሂደቶች በአምባገነኖች ጡጫ የሚዋዥቀው ሕዝብ ለውጥ ይፈልጋል::ለዚህ ለውጥ ደግሞ ሁላችንም በየፊናችን እየሮጥን ነው::ሲለን ተቧድነን ሲለን ተነጣጥለን ሲለን ተፈራርጀን ሲለን አሽሟጠን ሲለን ተሰዳድበን ሲለን ሲለን ሲለን .. ኧረ ስንት ጉድ አልፈናል::ካልፈው መማር ከጥፋታችን መታረም መፍትሄም ማበጀት ለትግሉ ጠቀሜታ አለው::አንዱን እየፈረጀ አንዱ ቢሮጥ ባለህበት እርገጥ ካልሆነ በስተቀር ምንም አይፈይድም ከወያኔ ምን እንማራለን?ልብ ብለን ከተመለከትን የወያኔ ካድሬዎች ከአንድ ፋብሪካ ተመርጦ የወጣ እባብ ይመስል ሁሉም አንድ አይነት መርዝ በኛ ላይ ይረጫሉ::እኛ ደሞ እርስ በርሳችን ስንበራረዝ ለነሱ በር በመክፈት መርዛቸው እናራባለን::ይህ መሆን የለበትም::እኛም ወያኔን ለመጣል እስከተነሳን ድረስ በጋራ ሆነን እርስ በርስ ሳኮራኮም ሳንፈራረጅ ከኛ በላይ ላሳር ሳንል መርዞቻችንን በጋራ ጠላታችን በሆነው ወያኔ ላይ መርጨት ያስፈልጋል::
ድርጅታዊ ዲሲፒሊን ግለሰባዊ ግብረገብነትን መተግበር ይጠበቅብናል::የለውጥ ፈላጊ ሃይሎች ነን ማለት ጠላታችን ወያኔ ነው ማስወገድ ያለብን ወያኔን ነው ማለት ነው::ቆም ብለን ረጋ ብለን ማሰብ አለብን::አንዱ የለውጥ ሃይል ሌላውን ቢንቀው ምንም የሚመጣ ለውጥ የለም ባለንበት ከመርገጥ ውጪ::አትኩሮታችን ሁሉ ወያኔን ማስወገድ ይሁን::እኛ የለውጥ ሃይሎች ስንባላ ወያኔ ስራዋን ትሰራለች::እኛ ስንተባበር ግን ወያኔ ያሰበችውን ሁሉ እናኮላሽባታለን::በየማህበራዊ ድህረገጹ ላይክ ኮሜንት እና ሼር ከመቁጠር ይልቅ ከመፈራረጅ ይልቅ እየፈረሰች ያለችውን አገር በጋራ እናቅና::በማይሆን ነገር ራስን ማጭበርበር ይብቃ::በጋራ በአንድነት እንቁም::መንቃት ያስፈልጋል::አትኩሮቶች ሁሉ ወያኔን እና የወያኔን እኩይ ተግባራት ወደ መደምሰስ ይሁኑ::በማይሆን አጀንዳ ተዘናግተን አንባላ::ሃገራችንን ከአውሬዎች እናድን::እንንቃ::ከባለፈው እንማር::አትኩሮቶች ሁሉ በወያኔ መደምሰስ ላይ ከሆኑ ተረባርበን በጋራ ከቆምን ከባለህበት እርገጥ ወጥተን አሸናፊነታችንን እናረጋግጣለን::ድል የሰፊው ሕዝብ ነው!!#ምንሊክሳልሳዊ