ሕወሓት የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጪ ግንባር አመራሮችን በአልሸባብ ቅጥረኞች እያስገደለ ነው::


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – የወያኔው ጁንታ በምስራቅ ኢትዮጵያ ባለበት ከፍተኛ ጦርነት ምክንያት ሊቋቋመው ያልቻለውን የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጪ ግንባርን አመራሮች በገንዘብ በመግዛት በሶማሊያ እና በምስራቅ ኢትዮጵያ አሉ የሚባሉ አመራሮችን እያስገደለ መሆኑ ከግንባሩ ተሰምቷል::ሕወሓት ከአልሸባብ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዳላት ተደጋግሞ የሚነገር ሲሆን አልሸባብን ብገንዘብ እንደምትገዛ እና በተለያዩ የሽብር ስራ ላይ እንደምታሰማራ መረጃዎች መለቅቅ ከጀመሩ ቆይተዋል::

ከግንባሩ ለምንሊክ ሳልሳዊ በኢሜይል የተላከው መግለጫ እንደሚያመለክተው ታፍነው የተወሰዱት የግንባሩ አመራሮች አቶ አብዱላዚዝ መሃመድ ዳሂር እና አቶ መኪ ኡመር አብዲ በአልሸባብ ታጣቂዎች ከተወሰዱ በኋላ ግንባሩ ጉዳዩን ሲከታተለው ቆይቶ አልሸባብ አመራሮቹን ከባይደዋ ሶማሊያ አፍኖ ወስዶ የት እንዳደረሳቸው አይታወቅም::ኦብነግ የሶማሊያ ውስጥ የሚንቀሳቀስ ፓርቲ አይደለም ያለው ግንባሩ በሶማሊያ ግጭት እጄ የለበትም ሲል ተናግሯል::አንዳን የሶማሊያ ባለስልጣናት እና የሶማሊያ ውስጥ ያሉ ታጣቂዎች የግንባሩን አባላት አፍነው በመውሰድ ለወያኔ መንግስት ያስረክባሉ ያሰቃያሉ ይገላሉ ሲል አምርሮ ገልጿል::

የግንባሩ የማእከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ አብዱላዚዝ መ.ዳሂር እና ቤተሰቦቻቸውን በጦርነት አጥተው ከኦጋዴን በመሰደድ በባይድዋ ያሉ ወላጅ አልባ ሕጻናትን የሚሰበስበው አቶ መኪ ኡመር አብዲ ሕጻናቱ በማጓጓዝ ላይ እንዳሉ ታፍነውበአልሸባብ ሚሊሻዎች ከባይደዋ ከተወሰዱ በኋላ የአልሸባብ ባለስልጣን ኢሳቅ ድሁሁሎ በሰጠው ትእዛዝ መሰረት አንገታቸውን ታርደው መገደላቸውን ግንባሩ አረጋግጧል::ይህ አልሸባብ የፈጸመው ግድያ የመጀመሪያ ባይሆንም ካሁን ቀደም የግንባሩን ወታደራዊ መሪ ኤሊያስ ሼ አሊ ን ጨምሮ ስምንት አመራሩን እንደገደለበት አትቷል::

የአልሸባብን ድርጊት ያወገዘው ግንባሩ የህ ሁሉ ግድያ እና ግፍ የሚፈጸመው አልሸባብ ከሕወሓት በሚቀበለው ትእዛዝ በገንዘብ ተገዝቶ መሆኑን እና የሕወሓት የጸጥታ እና ደህንነት ሃይሎች ከአልሸባብ ጋር በጋራ እደሚሰሩ አጋልጧል::ሕወሓት በፓርላማው ኦብነግን አሸባሪ ድርጅት ብሎ የፈረጀው ቢሆንም በተለያየ ጊዜ በእንደራደር ሲያጭበረብረው እንደነበር ሲታወቅ ከዚህ ቀደም ለድርድር ናይሮቢ ቀጠሮ ተይዞ ለድርድሩ የመጡትን አመራሮች ከናይሮቢ ያረፉበት ሆቴል አፍኖ ወደ አዲስ አበባ ማእከላዊ ወስዶ አስሮ እንደነበር ይታወሳል::‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

Minilik Salsawi's photo.