የዞን ዘጠኝ ጦማርያን የፍርድ ቤት ውሎ – የካንጋሮ ፍርድ ቤቱ ድራማ – ቀጠሮ ለ36ኛ ጊዜ ጳጉሜ 2 2007


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


የዞን ዘጠኝ ጦማርያን የፍርድ ቤት ውሎ (Update) #Freezone9bloggers

በዛሬው እለት የዞን ዘጠኝ ጦማርያን የወያኔ ካንጋሮ ፍርድ ቤት ቀርበዋል::አራቱ ጦማርያን በፍቃዱ:ናትናኤል:አቤል:እና አጥናፍ በጥቁር ሱፍ ደምቀው በፍርድ ቤቱ ተገኝንዋል::ንጽሕናቸውን በተለያየ መንገድ እየገለጹ ያሉት እና የፍርድ ቤቱን ነጻ አለመሆን በተግባር ያሳዩት ጦማርያን በራስ መተማመን ከፊታቸው ይነበባል::ወደ ችሎቱ 84 ሰዎች ገብተዋ የፍርድ ሂደቱን እየተከታተሉ ነው::

ዳኞቹ አርፍደዋል:: በችሎቱ ውስጥ ዝምታ ሰፍኗል:: የፍርድ ቤቱ ጠባቂ ፖሊስ ከችሎቱ መግቢያ ጠረጴዛ ላይ ጣፋጭ እንቅልፍ ተኝቷል::በችሎቱ ውስጥ ያሉ የጦማሪያኑ ደጋፊዎች ዲፕሎማቶች እና ጋዜጠኞች ዳኞቹ እስከሚመጡጡ በሚል ይመስላል በዝግታ እያወሩ የችሎቱን ጸጥታ በንግግር ትንሽ ሞቅ አድርገውታል::

ዳኞቹ አልገቡም ::የዞን ዘጠኝ ጦማርያን ጠበቆቻቸው ወደ ቢሮ ተጠርተው ገብተዋል:: ጦማርያኑ ከጀርባ በር በኩል እንዲቀመጡ ተደርገዋል:: ዳኞቹ ችሎት ሳይሰየሙ ከጀርባ ሆነው የሚሰሩት ድራማ ሰዉን አስጨንቆታል::የካንጋሮ ፍርድ ቤቱ ድራማ ቀጠሮ ለ36ኛ ጊዜ ጳጉሜ 2 2007 ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል።