ትኩረት ለሚገባቸው ጉዳዮች ትኩረት እንስጥ::መዘናጋት እና አቅጣጫ መሳት ይቁም::
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
ለውጥ የሚጠላ ማንኛውም ሰው የለም:; ለውጥ የማይፈልግ ካለ አንድም ከአምባገነን ስርአቶች የተዳቀለ አሊያም የጥቅሞችን ማግበስበስ የለመደ ስግብግብ የሕዝብ ጠላት ብቻ ነው::በኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ ያስፈልጋል;ይህ ደግሞ ሳይታለም የተፈታ ነው::በስልጣን ላይ ያለው አመራር አስተዳደሩ የተበላሸ ስለሆነ ለውጥ ለማምጣት የማይችልበት ደረጃ ላይ ከመድረሱም አልፎ ተኮላሽቷል::ስለዚህ ለውጥ ማምጣት የሚቻለው ይህንን የተኮላሸ አምባገነን ስርአት በማስወገድ አዲስ ስርአት መፍጠር ሲቻል ብቻ ነው::ይህንን የማስወገድ እርምጃ መውሰድ የሚቻለው ደግሞ ትኩረት ለሚሰጣቸው ጉዳዮች ትኩረት ስንሰጥ ብቻ መሆኑን ማወቅ ያስፈልገናል::
እስካሁን ባለው የትግል ሂደት ውስጥ ራሳችን እያገዘፍን ራሳችን እያደባየን ከፍ ስንል እየተንቀባረርን ዝቅ ስንል ደሞ እየተኮማተርን ለአምባገነኡ እድሜ መርዘም ራሳችን አስታውጾ ማድረጋችን መካድ የለብንም::ጥፋቱን ያመነ መፍትሄ ስለማያጣ ለትግሉ አትኩሮት ሰጥተን ከመታገል ይልቅ እርስ በርስ መጠላለፍ ጆሮ ዳባ ልበስ ማለት ያልበሰሉ ካድሬዎችን ተጠቅመን በስድብ እና በዝርጠጣ ስም በማጥፋት እና በትንኮሳ ላይ መሰማራት የወያኔ አቅጣጫ ማስቀየሻ ስልቶችን ተቀብሎ እንደ ገደል ማሚቶ ማስተጋባት ወያኔን ለመደምሰስ ከተነሱ የለውጥ ሃይሎች ላይ ተቻችሎ አለመቀጠል ወያኔ በሚሰጠው የቤት ስራ ላይ በጋራ ሆነን እየተቀባበልን ማዛጋት እና መዘናጋታችን ትኩረት ለሚገባቸው ጉዳዮች ትኩረት እንዳንሰጥ መንገዱን ቀርቅረን ይዘናል::
ወደ መፍትሄ እና እንደ ሕዝብ የውሳኔ ሰጪነት መስመር ውስጥ ለመግባት አንድነት ሰላም እና ፍቅር መቻቻል መመካከር እና መድማመጥ ይፈለግብናል::በአሁን ወቅት የሚያስፈልገው ምንድነው የሚለውን ማወቅ ያስፈልጋል::ወያኔን ለመደምሰስ ለትግሉ አትኩሮት መስጠት አስፈላጊ ወቅት ላይ ነው::ለየትኛው ትግል? እያንዳንዳችን ላመንነበት ትግል አስፈላጊዉን ትብብር እና ድጋፍ ማድረግ ከቻልን ከሌሎች ወያኔን ለመደምሰስ ከተሰማሩ ሃይሎች ጋር አብሮ መስራት ባይሆንልን እንኳን በመቻቻል እያለፍን አስፈላጊውን የአቅም መስዋትነታችንን ወደ ተግባር ማሳደግ እችላለን::ሌላው ስድብ ስም ማጥፋትና ዝርጠጣ ሊቆሙ የሚገባቸው የትግል ስልቶች ናቸው::በስድብ ስም በማጥፋት እና በዝርጣጣ ምንም የምናመጣው ለውጥ የለም::ያልበሰሉ ካድሬዎች በባዶ ሜዳ ያወቁ መስሏቸው ሊፈራገጡ ይችሉ ይሆናል::እነሱን ተከትለው ደሞ አስመሳዮች ቅጥረኞች አዛኝ ቅቤ አንጓች መስለው ሊዘባርቁ ስለሚችሉ ጥንቃቄ መወሰድ ያለበት ከለውጥ ሃይሎች ጉያ መሆን ይገባዋል::በአሁኑ ወቅት ትኩረት የሚገባቸው ጉዳዮች በለውጥ ሂደቱ ላይ የሚድረጉ ትግሎችን አጠናቅረን በየቦታው የሚደረጉ የትግል ስራዎችን በማቀናጀት ወደፊት ልንገሰግስ ይገባል::ለወያኔ እና ተላላኪዎቹ የቤት ስራ ትኩረት ሳንሰጥ ለለውጥ ትግሉ ስኬት የዜግነት ድርሻችንን ልናበረክት ይገባል::#ምንሊክሳልሳዊ