የዓለማችን አማካይ ሙቀት ጨመረ (ወርቁ ለገሠ)


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


አንድ መቶ ስልሳ ዓመት (1850 ዓ.ም) አንስቶ የተመዘገበውን የዓለማችን አማካይ ሙቀት መሠረት በማድረግ ያለፈው 1998 ከፍተኛው ሙቀት የተከሰተበት ሲሆን 2010 ደግሞ ሁለተኛ ሆኗል። የብሪታኒያ ኢንስቲትዩት ሰሞኑን እንዳስታወቀው ይህ መረጃ የዓለም አየር ንብረት ቀስ በቀስ እየተዛባ መምጣቱን ይጠቁማል ብሏል። ከታች ሥዕሉ እንደተመለከተው ከዓለማችን አማካይ ሙቀት ጋር ሲነፃፀር 1998 ከ0.5 ድግሪ ሴንቲግሬድ፣ 2005 ደግሞ ከ0.47 በላይ ተመዝግቦባቸዋል።፡ፊል ጆንስ የተባሉት የብሪታኒያ የአየር ንብረት ምርምር ዳይሬክተር እንደሚሉት ከሆነ ያሳለፍነው ዓመት ከ1961-1990 የነበረውን አማካይ ሙቀት በ0.5 ብልጫ አሳይቷል።

በብሪታኒያ የአየር ንብረት የሚከታተለው ኢንስቲትዩት በዓለም ካሉት 3 ግዙፍ ማዕከላት አንዱ ነው። ሁለቱ የሚገኙት እዚህ ዩናይትድ ስቴትስ ሲሆን እነሱም በበኩላቸው 2010 እጅግ ሞቃት ከሚባሉት ውስጥ ይመደባል ብለዋል። በዚህ መረጃ መሠረት ከ2008 በስተቀር ከ2001-2010 የነበሩት ዓመታት ከፍተኛ ሙቀት ከታየባቸው ከ1-10 ባለው ደረጃ ውስጥ ይካተታሉ። ይህ የሚያሳዬው በግሪን ሀውስ ጋዝ ምክንያት ዓለማችን ከወትሮው እየሞቀች መምጣቷን ነው።

የዓለምን አማካይ ሙቀት ለመቀነስ የሚደረገው ትግል በተፈጠረው የምጣኔ ሃብት ቀውስ የተነሳ ለአማራጭ ሃይል ምንጭ ፍለጋ የሚመደበውን መዋዕለ ንዋይ ክፉኛ የጎዳው ከመሆኑም ባሻገር የዓለም መንግሥታት በ2012 ዓ.ም. የሚያበቃውን የኪዮቶ ስምምነት ሊተካው የሚችል ተቋም ሳይመሠረቱ ተበትነዋል።


ያም ሆነ ይህ አሁን የተገኘው መረጃ ሰው ሠራሽ የአየር ንብረት መዛባት መላ ምት ሳይሆን ገሃዳዊ መሆኑን ያጠናክራል ተብሏል።

የአየር ንብረት መዛባት ባስከተለው ተፅዕኖ ምክንያት ሩሲያ፣ ቻይናና አርጀንቲና በድርቅ መጎዳታቸውን ተከትሎ የምግብ ዋጋ ግሽበት ታይቷል። ባለፈው ዓመት ደግሞ ፓኪስታንና ቻይና በከባድ ጎርፍ ክፉኛ መመታታቸው የአየር ንብረት መዛባት ጦስ የት እየለሌ መህኑን ያስረዳል።

የአየር ንብረት መዛባት የሚያስከትለው ሙቀት ብቻ አይደለም። ለምሳሌ አንዳንድ የአውሮፓ፣ ራሽያና የዩናይተድ ስታተስ ግዛቶች በ2010 ከፍተኛ ቅዝቃዜ ተከስቶባቸው ነበር።

ባለፈው ወር በካንኩን ሜክሲኮ የተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ስብሰባ የአየር ንብረት መዛባት ለሚያጠቃቸው ድሃ አገራት ገንዘብ ለማሰባሰብ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ነገር ግን የኪዮቶውን ስምምነት ተክቶ የአየር ብከላን ለመቀነስ የበለፀጉ አገሮች መውሰድ የሚገባቸው ዕርምጃ ተቀባይነት አላገኘም።


በርግጥ መንግሥታት በካንኩን ስብሰባቸው ላይ የዓለም አማካይ ሙቀት ኢንዱስትሪዎች ከመስፋፋታቸው በፊት ከነበረው ሙቀት ቢበዛ ከ2 ድግሪ በላይ መጨመር እንደማይኖርበት ተስማምተዋል። ነገር ግን ስምምነቱን በተግባር ለመተርጎም እያንዳንዱ አገር ሊወስደው የሚገባ ዕርምጃ በግልፅ ስላልተቀመጠ የተፈለገውን ለውጥ ማምጣት አስቸጋሪ ይሆናል።

ይህ በ እንዲህ እንዳለ የዓለም የሃይል ምንጭ ሥጋት ዝቅተኛ ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ አማራጭ ምንጮችን ለማፈላለግ መዋ ዕለ ንዋይ መፍሰሱ አይቀርም፣ ይህም እግረ መንገዱን የአየር ንብረት መዛባትን ሊቀንስ ይችላል የሚል ተስፋ አለ።

ምንጭ፡ ሬውተርስ የዜና ወኪል