የፖለቲካ ነጻነትና የሲቪል መብት ንፅፅር
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
ፍሪደም ሀውስ የተሰኘው ግብረ ሠናይ ድርጅት የ2010 ዓለማቀፋዊ የፖለቲካ ነጻነትና የሲቪል መብት መከበር አስመልክቶ በ194 አገሮች ላይ ያካሄደውን ጥናት ይፋ አድርጓል። ከፍተኛ የፖለትካ ነጻነትና የሲቪል መብቶች ጥሰት የሚታይባቸው አገሮች 7 ነጥብ ሲሰጣቸው በአንፃሩ ከፍተኛ የፖለቲካን የሲቪል ህብረተሰብ ነፃነት የተከበረባቸው ደግሞ 1 ነጥብ ያገኛሉ። በዚህ ነጥብ አሰጣጥ መሠረት ከ1-2.5 ሙሉ ነፃነት፣ ከ3-5 በከፊል ነፃ ከ5.5-7 ደግሞ ነጻነት የሌላቸው ሃገራት ምድብ ውስጥ ይካተታሉ።
ቀጥሎ በተመለከተው ሥዕላዊ መረጃ ለምሳሌ ጋና በፖለትካ ነፃነት 1 በሲቪል ደግሞ 2 በማግኘት በአፍሪካ አህጉር ውስጥ የምትገኝ የነፃነት ማማ ሆናለች። በአንፃሩ የኢሳያስ አፈወርቄ ኤሪትራ 7 ነጥብ በማስቆጠር የተመልካችን ቀልብ ብትስብም አሃዙ ያዘለው መል ዕክት የተገላቢጦሽ እንዲሆን በመደረጉ በነፃነቱ ውድድር ተሳትፍዋ ሁራ ወጥታለች። ኢትዮጵያ በመለስ ዜናዊ አስተዳደር ሥር መንግሥታዊ መዋቅር እምብዛም ከሌላት የሶማሊያ ክፋይ አቻ መውጣቷ የመንግሥትን አስፈላጊነት በጥያቄ ቀለበት ውስጥ እንድወድቅ አድርጎታል።
ይህን መረጃ መሠረት በማድረግ የኢትዮጵያን መፃዔ ዕድል በመጠኑም ቢሆን መተንበይ ይቻላል። በ2011 ኢትዮጵያ ሶስት አማራጮች አሏት። አሁን ያገኘችውን 5 ነጥብ ሳትነጠቅ መቀጠል፣ ወይም 2.5 ነጥብ በመቀነስ ነፃ ተብለው ከተፈረጁት አገሮች ተርታ መሰለፍ፣ ሶስተኛው ደግሞ 0.5 ነጥብ ብቻ በማግኘት ከእህቷ ኤርትራ ጋር መቀላቀል። አሁን ያለው የፖለቲካ ትኩሳት የሚለካው ቴርሞ ሜትር እንደሚያሳየው ባዙቃው ወደላይ እንጅ በፍጹም ወደታች የሚወርድበት ሁኔታ አይታይም። ስለዚህ 0.5 ጭማሪው ቀላልና ሊሳካ የሚችል በመሆኑ ኢትዮጵያ ሶማሌን በፎርፌ አሸንፋ ከ ኤርትራ ጋር አቻ ልትሆን እንደምትችል ለመተንበይ ነቢይ መሆን አይጠይቅም።
ወርቁ ለገሠ (01/06/11)