የዶክተር ብርሃኑ ጥሪ! (ከተ.ገ.)


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


የነሱን ቢራ ከምትጠጣ ለነፃነትህ ውሃ ጠጣ!!

እንግዲህ ይሄ ዳሸን ቢራና ፔፕሲኮላን የሚመለከት ሊሆን ይችላል።

እነሱ ያመረቱትን ከምትለብስ የተቀደደ ልብስ ልበስ!

የአልመዳ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ Made in USA የሚል ታግ እየለጠፈ የአዲስአበባን ገበያዎች ማጥለቅለቁን ያውቃሉ? ከዱባይ ኮንቴይነር እያስጫኑ፣ ያለቀረጥ እያስገቡ ትርፍ ስለሚዝቁ የወያኔ ሰዎችስ ሰምተዋል?

በነሱ ሲሚንቶ ከምትገነባ ሆን ብለህ ሌላ መንገድ ፈልግ! ወይም ግንባታውን ለጊዜው አዘግይ!

የወያኔው የመሶቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ አትራፊ እንዲሆን የሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ ከአቅም በታች እንዲያመርት ተደርጓል። የሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ የቦርድ ሊቀመንበር ደግሞ ስዩም መስፍን ነው። የሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ ኢንጂንየር የወያኔን ሸር በመቃወሙ 5 አመት መታሰሩንስ ያውቃሉ? ሌላም ልጨምርሎት። ባንድ ወቅት የሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካን ለመጠገንና ለማስፋፋት ኮንትራት ፈርሞ ሊመጣ የነበረውን ጀርመናዊ ኢንጂንየር፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ቪዛ ስለከለከለው የማስፋፋትና የጥገና ፕሮጀክቱ ተቋርጦአል። ሙገር ይህን መስዋእትነት የሚከፍለው፣ መሶቦ ሲሚንቶ አትራፊ አንዲሆን ነበር።

የመንግስት ሰራተኛ የሆንሽ በስራሽ ላይ ለግሚ! በቀን ሰርተሽ የምትጨርሺውን ስራ ሳምንት አቆይው።

ይሄ ጥሪ ተግባራዊ መሆን ሲጀምር ወያኔ ተሽመድምዶ እጁን ይሰጣል። ማህተማ ጋንዲ በዚህ የትግል ዘዴ ህንድ የተባለች ሃገሩን ነፃ ማውጣቱ የሚታወስ ነው።

በመስሪያ ቤትሽ የሚደረገውን የዘረፋ ምስጢር፣ ወይም ማናቸውንም ይጠቅማል ብለሽ የምታስቢውን መረጃ፣ ለነፃነት ታጋዮች አሳልፈሽ ስጪ፣

እያንዳንዱ ዜጋ ለሃገሩ ሰላይ ከሆነ ድል ቅርብ ይሆናል። በመጨረሻ የሚያሸንፈው ጥሩ የተመገበው ሳይሆን፣ በቂ መረጃ ያለው ሃይል ብቻ ነው።

(የዶክተር ብርሃኑን ጥሪ ሙሉውን ለማዳመጥ www.ginbot7.com ይጎብኙ!)