አቶ ጁኔዲን ሳዶ ለመጀመሪያ ጊዜ ህወሓት ላይ ቦምብ ወረወረ።
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።

አቶ ጁኔዲን ሳዶ
አቶ ጁኔዲን ሳዶ ለመጀመሪያ ጊዜ ህወሓት ላይ ቦምብ ወረወረ። #VOAafaanOromoo
“የኦሮሞ ህዝብ ይህ ስርዓት የኛ ስርዓት አይደለም እያለ ሲጮህ አሳምኜ እንዲቀበሉ ማድረጌ የኦሮሞን ህዝብ እጅና እግሩን አስሬ እሳት ውስጥ እንደጨመርኩ ይሰማኛል፣ ይህን በማድረጌ የኦሮሞን ህዝብ ይቅርታ እጠይቃለሁ።
ኦህዴድ ስልጣን የለውም፣ የራሱ አጀንዳ የለውም፣ የኦህዴድ ፕሮግራም የተፃፈው በህወሓት ነው። የኦህዴድ ፕሮግራም የህወሓት ፕሮግራም ኦሮሚኛ ቅጂ/version ነው። የኦሮሞ ጥያቄ በኦህዴድ ሊፈታ አይችልም። ማስተር ፕላን የኦህዴድ አይደለም።
የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ ራስን በራስ የማስተዳደር ነው። የኦሮሞ ጥያቄ የሀገር ባለቤትነት ጥያቄ ነው። የኦሮሞ ጥያቄ የነፃነት ጥያቄ ነው።
ግንዱን ትቶ ቅርንጫፎቹን ማራገፍ ፋይዳ የለውም። ችግሩ ያለው ግንዱ ላይ ነው። የህወሓት ስርዓት መወገድ አለበት።”
Finfinne Post