ሻንበል ከበደ አስረስ የአማራ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ከ2ሺህ ተሰብሳቢ ድምፁን አስከብሮ በልዩነት የወጣ ብቸኛ የብአዴን አመራር


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


Image may contain: 1 person , suit

ሻንበል ከበደ አስረስ ተሰብሳቢውንም ሰብሳቢውንም ያቁነጠነጠ ጀግና

ሻንበል ከበደ አስረስ የአማራ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ከ2ሺህ ተሰብሳቢ ድምፁን አስከብሮ በልዩነት የወጣ ብቸኛ የብአዴን አመራር

ይህ ግለሰብ ታሪኩም እንደዛሬው ገድሉ የሚያስደምም ነው አሉ። ተሰብሳቢውንም ሰብሳቢውንም ያቁነጠነጠ ጀግና።
ብአዴን ያዥጎደጎደውን የአንድ አመት የስልጠና ማንዋል የሚመስል የአቋም መግለጫ አልቀበልም በማለት ድምፄን በልዩነት መዝግቡልኝ ብሎ አማራዊ ክብሩን ያስጠበቀ ወንድ።
አረንዛው ዳሞቴ የህወሃትን የበላይነት በማስረጃ የሞገተ፣የትግራይን እና የአማራን የኢኮኖሚና ፖለቲካ እንዲሁም ማህበራዊ ዘርፍ የእድገት ልዩነት በራሳቸው ሪፖርት መረጃን እየተነተነ ሰብሳቢዎቹን ምላሽ ያሳጣ እውነተኛ የህዝብ ልጅ ነው።

በተለይም በመንገድልማት፣ በኮንስትራክሽን፣ በቴሌ፣በ ደህንነት፣በመከላከያ ፣በኢኮኖሚው ዘርፍ…..የህወሃትን በዝባዥ የበላይነት በደንብ ያሳየ ነው።ይህ ሰው ልበ ሙሉና አንደበተ ርቱዕ ነው።ወልቃይት ደም ታፋስሳለች ያለ ቅድመ ሁኔታ ወደ አማራ ትመለስ በማለት ቀጭን ትዕዛዝ መሰል አስተያየቱን የሰነዘረ ነው።
.ይህንን ሁሉ ከተናገረ በኋላ አሽከሩ ብአዴን የህወሃት የበላይነት አለመኖሩን፣የአማራ ተጋድሎ የፀረ ሰላምና ትምክህቶች ነው….ብሎ ሲያነበንብ ሻንበላ ሆየ እኔ የለውበትም ከዚህ መግለጫ ብሎ በአቋሙ ፀና ።