ዩናይትድ ስቴትስ የኢትዮጵያ መንግሥት በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የወሰደው የሀይል እርምጃ መፍትሄ አይደለም አለች


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


ዩናይትድ ስቴትስ የኢትዮጵያ መንግሥት በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የወሰደው የሀይል እርምጃ መፍትሄ አይደለም አለች

በኢትዮጵያ እየተወሰዱ ያሉት የሀይል እምጃዎችና ሌሎቹ ለሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ መፍትሄ ሊሆኑ አይችሉም ሲሉ በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ረዳት ሚኒስቴር ቶም ማሎንስኪ አስታወቁ።

ረዳት ሚኒስትሩ እንዳሉት የፀጥታ ሀይሎች ከመጠን ያለፈ ሀይል መጠቀም በርካታ ሰዎችን መግደል እና ማቁሰል እንደዚሁም በሺዎች የሚቆጠሩ ማሰር ቀጥለዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ሰላማዊ ሰልፎቹ ሰላማዊ አልነበሩም ብሏል።

ከሰልፎቹ ጥቂቶቹ ለብጥብጥ መሳርያነት ጥቅም ላይ ውለው ይሆናል ያሉት በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መስርያ ቤት የዲሞክራሲ የሰብዓዊ መብቶች እና የሥራ ጉዳይ ረዳት ሚኒስትር ቶም ማሎስኪ አብዛኛዎቹ የሰልፉ ተሳታፊዎች ግን በኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥት የሰፈረውን ሃሳብ የመግለፅ መብት የተጠቀሙ እንደነበር እናምናለን ብለዋል።

ኢትዮጵያ የውጭ ስጋቶች እንዳሉባት እንደሚረዱም ጠቅሰዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

http://av.voanews.com/clips/VAM/2016/08/22/541444a9-7576-410c-9af4-8dd125c60e24.mp3

በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መስርያ ቤት የዲሞክራሲ የሰብዓዊ መብቶች እና የሥራ ጉዳይ ረዳት ሚኒስትር ቶም ማሎስኪ