ቅዳሜ በሐምሌ 30 የወያኔ መንፈስ በደብረታቦር ይባረራል፤ ባነሮች በሚገባ ተዘጋጅተዋል። ትግሉን እንደጀመርነው እንጨርሰዋለን፤
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።

“ትግሉን እንደጀመርነው እንጨርሰዋለን” ዐማሮች በደብረታቦር ከተማ
_ነገ በተጠራው የወይኔዎች ስብሰባ ሕዝቡ እንዳይተባበር አስተያየት ተሰጥቷል፤
ቅዳሜ በሐምሌ 30 የወያኔ መንፈስ በደብረታቦር ይባረራል፤ ባነሮች በሚገባ ተዘጋጅተዋል። ትግሉን እንደጀመርነው እንጨርሰዋለን፤ ወልቃይት ጠገዴ፣ መተከል፣ ራያ ዐማራ ነው፤ በአባቶቻችን አገር ግዞተኛ አንሆንም… ወዘተ የሚሉ ደማቅ ባነሮች ተዘጋጅተዋል። ወልቃይት ጠገዴና ኮሎኔል ደመቀ የተጋድሎው ማእከል ሆነዋል።
በተያያዘ ዛሬ የከተማው ከንቲቫ ጽ/ቤት የባጃጅ ሾፌሮችን ስብሰባ ጠርቶ ሰልፉን እንዳይተባበሩ ቢጠይቅም ስብሰባ አቋርጠው መውጣታቸው ትውቋል።
ነገ ብአዴን የከተማውን ሕዝብ በየቀበሌው ስብሰባ የጠራ ሲሆን ማንም ወደ ስብሰባ እንዳይሄድ የዐማራ ተጋድሎ አስተባባሪዎች በጥብቅ አሳስበዋል።

(የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የነበሩ፣ ነጋዴዎችና የመንግሥት ሠራተኛ ሆነው በስለላ ወገኖቻችን የሚያስበሉ ሰዎች ስም ዝርዝርና ፎቶ ግራፍ ደርሶናል፤ እነዚህን ግለሰቦች ይፋ የምናደርግ ሲሆን ከእኩይ ሥራቸው ካልተመለሱየዐማራ ሕዝብ ምርታቸውን እንዳይጠቀሙም አሳስበዋል)
የዐማራ ተጋድሎ ያሸንፋል! Muluken Tesfaw
