የወያኔ መንግስት እስረኞችን ለማሰቃየት በቃሊቲ እስር ቤት 4 የጨለማ ክፍል እንዳሰራ ታወቀ ።


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


የወያኔ መንግስት እስረኞችን ለማሰቃየት በቃሊቲ እስር ቤት 4 የጨለማ ክፍል እንዳሰራ ታወቀ ።

የወያኔ መንግስት በእስር ቤት ያሉትን የፖለቲካ እስረኞች ለማሰቃየት በቃሊቲ እስርቤት ውስጥ 4 የጨለማ ክፍሎችን እንዳስገነቡ ምንጮቻችን ዘገቡ ።

ከዚህ በፊት በቃሊቲ እስርቤት ውስጥ ጨለማ ክፍል ስድስተኛ ተብሎ በሚጠራው ቦታ አንድ ብቻ የነበረ እና እሱን አፍርሰው በአሁኑ ሳአት 4 ክፍል በመገንባት በእስረኞቹ ላይ ከፍተኛ ስቃይ እና እንግልት ለማድረስ በቁርጠኝነት መነሳቱ የሚያሳይ ነው ።

አሁን በአዲስ መልክ የተገነባው የጨለማ ክፍል እያንዳዱ 36 ሰዉ እንደሚያዝ ለማወቅ ተችሎዋል ።

በተያያዘ ዜና በቃሊቲ እስር ቤት የሚገኙ በፖለቲካ እስረኞች ላይ የሚደረገው ጫና እንደቀጠለ ሲሆን ከትላንት ጀምሮ ከእናት አባት እና ልጅ ውጭ የትኛውም ዘመድም ሆነ ወገን እንዳይጠይቃቸው እንደተከለከሉ ምንጮቻችን ከስፍራው ዘገቡ ።

መላው ማህበረሰብ በጨቁዋኙ በወያኔ መንግስት ላይ በአንድነት በመነሳት ጭቆናን እንዲታገሉ ጥሪ ቀርቦዋል ።