እርምጃ ይወሰድባቸዋል (ትረሸናላችሁ) ከተባሉ መካከል የሰባ እስረኞች የስም ዝርዝር ቃሊቲ እስረኞች ቦርድ ላይ ተለጥፏል፡፡
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
እርምጃ ይወሰድባቸዋል (ትረሸናላችሁ) ከተባሉ መካከል የሰባ እስረኞች የስም ዝርዝር ቃሊቲ እስረኞች ቦርድ ላይ ተለጥፏል፡፡ ==================================================================
የቃሊት መረሚያ ቤት ሊረሽናቸው የፈለገውን ታራሚዎች የስም ዝርዝር በገሃድ ለጥፎታል።
የቃሊት ከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ቤት አድማ አስነስተዋል ወይም ለማምለጥ ሞክረዋል የሚል ሰበብ በመፍጠር እንደ ልማዱ ለመረሸን ያዘጋጃቸውን የሰባ የህግ ታራሚዎች የስም ዝርዝር በቀድሞ አጠራር ዞን አንድ የታራሚዎች ማስታወቂያ ቦርድ ላይ ፣የ84 ታራሚዎች የስም ዝርዝር በዞን ሁለት የታራሚዎች ማስታወቂያ ቦርድ ላይ ለጥፏል፡፡ ከነዚህም መካከል የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል የሆነው የአህመዲን ጀበል ስም ይገኝበታል፡፡
ይህንን ለማረጋገጥ የሚፈልግ የስራ ሃላፊ ወይም ባለ ስልጣን የቀድሞ ዞን አንድ እና ዞን ሁለት ውስጥ ገብቶ በማስታወቂያ ቦርዱ ላይ ማየት እንደሚችል ከማረሚያ ቤት የደረሰን መረጃ ያሳያል።
በማስታወቂያ ቦርዱ ላይ የስም ዝርዝራቸው የወጣው በግፍ የታሰሩ 1 /የአማራ ክልል ተወላጆች 2 /የኦሮሞ ክልል ተወላጆች 3 / የደቡብ ክልል ተወላጆች ናቸው፡፡
በዚህ ዝርዝር ውስጥ ትግርኛ ተናጋሪ ታራሚዎች አልተካተቱም ። በዚሁ ቃሊቲ ማረሚያ በ1998 የተነሳውን ሀገር አቀፍ ተቃውሞ ተከትሎ በዚህ አይነት የዘር ጥላቻ ቁጥራቸው ብዙ የሆኑ ታራሚዎች ረብሻቹሃል በሚል ሰበብ መረሸናቸው የሚታወቅ ነው።
አሁኑም በህዝበ ሙስሊሙ የገቡ ታራሚዎች፣ በኦነግ ስም የታሰሩ፣በግንቦት 7 እና በአርበኞች የታሰሩ ታራሚዎች እና ከነሱ ጋ ይበላሉ ይጠጣሉ ወይም ይጫወታሉ የሚሉዋቸውን ታራሚዎች በመቀላቀል የበቀል ስሜት የወለደውን የጥፋት እርምጃ ለመውሰድ ተዘጋጅተዋል።
በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ውስጥ ዋናው አስተዳዳሪው ፣ የጥበቃ እና ደህንነት ሃላፊው የደህንነት መዋቅሩ ውስጥ ያሉ ሃላፊዎች ፣ የዞን ተጠሪ ፣ የሽፍት መሪ ፣ የህክምና ክፍል ነርሶች ተብለው የተመደቡት ባጠቃላይ ትግሬዎች ናቸው። በቃሊቲ ውስጥ ኦሮሞ አልያም አማራ ኮሎኔል ሻለቃ ወይም መቶ አለቃ በትግሪኛ ተናጋሪ ተራ ወታደር የሚታዘዝ ነው።
የቃሊቲ ማረሚያ ቤት የተደራጀ ፣ህውሃት ከየ ክልሉ የሚፈልጋቸውን ሰዎች የሚያጉሩበት እስር ቤት ነው ። የህወሀት መንግስት አሁን እስረኞችን ለመረሸን የተነሳው በተለይ በአሁኑ ሠዐት በተለያዩ አካባቢዎች የተነሳበትን ተቃውሞ ማስተንፈሻና መበቀያ ነው።
