መፍረስ ያለበት የፍትሕ ሚኒስቴር ሳይሆን ሕወሓት የሚባለው ገዳይ ድርጅት ነው::


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


መፍረስ ያለበት የፍትሕ ሚኒስቴር ሳይሆን ሕወሓት የሚባለው ገዳይ ድርጅት ነው::

ምንሊክ ሳልሳዊ – ከነሰው በላዎቹ ከነአዘናጊዎቹ ከነገዳዮቹ መንደር የሚመጡ የጊዜ መግዣ እና ማጭበርበሪያ ዘገባዎች አሁንም አልቆሙም:: የኢትዮጵያ ሕዝብ ካለምንም የፖለቲካ ድርጅት ይሁን አስተባባሪ ተቋም መሪነት በራሱ ስለመብቱ እና ነጻነቱ አደባባይ በመውጣት እየተገደለ እየቆሰለ በመፋለም ላይ ይገኛል::በአሁን ወቅት የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚፈልገው ስር ነቀል ለውጥ ነው:: የፍትሕ ሚኒስትር መፍረስ የሃሰት ክስ ፋብሪካ አቅቢ ሕግ መቋቋም አሊያም የጸረ ሙስና ኮሚሽን ስልጣን ተገፎ ኮሚሽኑ ውደ ትምህርት ቤትነት መለወጥ አይደለም::ሕዝቡ የሚፈልገው ገዳይ ማፊያ የሆነው ሕወሓት እንዲፈርስለት ብቻና ብቻ ነው::

ፍትህ ተቀብሯል::ለዘላቂ ልማት እንሰራለን በሚል ስርኣት ውስጥ የመሰረታዊ የዲሞክራሲ መብቶች በጊዜያዊነት መኖር እና እንደመነገጃ መጠቀም ህዝብን አገለግላለሁ ሳይሆን አጭበረብራለሁ እንደማለት ይቆጠራል:: የወያኔ ስርኣት ባለስልጣናት በፍርሃት ተውጠው በጠበንጃ ሃይል በሚኖሩባት በዚች ኢትዮጵያችን የፍትህ እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ አሁንም እጅግ መልስ የሚያሻቸው ጉዳዮች ናቸው::ዜጎች በሃገራቸው እንዳይኮሩ በመኖር ደህንነታቸው ላይ ጥርጣሬ እንዲያሳድሩ እየተደረገ ስለሆነ ይህ ደሞ ወያኔ የያዘውን ስልጣን ላለመነጠቅ የሚሰራው ፖለቲካዊ ደባ ውጤት መሆኑ እሙን ነው::

ህዝብ ባለው ስርኣት ላይ እምነት የለውም:;በሃገራችን የተንሰራፋው አገዛዝ በከፍተኛ ደረጃ በፍርሃት በመዋጡ የፍትህ ተቋማቱን ሁሉ በቁጥጥር ስር አውሎ ዜጎችን የሚያጠቃበት የፖለቲካ ዱላ አድርጎታል:: ከባዶ ተነስተው ቢሊየነር የሆኑ ባለስልጣናትን እና ዘመዶቻቸውን ይቆጣጠራል ያጋንጣል የተባለው የጸረ ሙስና ኮሚሽን ከጠያቂነት ወደ አስተማሪነት እንዲሸጋገር ተፈርዶበታል::የሃሰት ክስ የሚፈበርከው አቃቢ ሕግ በሕወሓት ተጠፍጥፎ ስለተሰራ ተቃዋሚዎችን በመፈረጅ እና በመወንጀል ያስራል ያንገላታል ማለት ነው::ህጎች በተግባር ህዝብን አለማገልገላቸው እና በባለስልጣናት የመደፍጠጣቸው ውጤት ነው::ፍትህ እና መልካም አስተዳደር እንዴት ሊረጋገጡ ይችላሉ በዚህ ሁኔታ ውስጥ እየተጓዝን ነው ጥያቄያችን ስለዚህ ህዝብ ለውጥ ይፈልጋል::መፍረስ ያለበት የፍትሕ ሚኒስቴር ሳይሆን ሕወሓት የሚባለው ገዳይ ድርጅት ነው:: #MinilikSalsawi