የተባበሩት መንግስታት ሶሪያና ኢትዮጵያን በአንድ ምድብ አስቀምጧል : በሁለቱ አገራት ያለው ሁኔታ ለህፃናት አስፈሪ ሆኗል ::
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
የተባበሩት መንግስታት ሶሪያና ኢትዮጵያን በአንድ ምድብ አስቀምጧል : በሁለቱ አገራት ያለው ሁኔታ ለህፃናት አስፈሪ ሆኗል ::

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በኢትዮጵያ የቅርብ ዓመታት ታሪክ ውስጥ እጅግ ከፍተኛው በመሆን የተመዘገበው ድርቅ 400.000 ህፃናትን ለአልሚ ምግብ እጦትና 10 ሚልዩን የሚደርሱ ሰዎችን ለምግብ እርዳታ ፈላጊነት ዳርጓቸዋል ብሏል ።
ድርጅቱ በሶስት አስርት ዓመታት ታሪኳ አስከፊው ድርቅ በመሆን የተመዘገበባት ኢትዮጵያ መጥፎውን ጊዜ እንድትቋቋም የ50 ሚልዮን ዶላር እርዳታ ከለጋሾች ጠይቄላታለሁ ማለቱን አልጀዚራ ዘግቧል ።
ሴቭ ዘ ችልድረን በመግለጫው በኢትዮጵያ የተከሰተው ድርቅ ልክ በሶሪያ ያለው ጦርነት ለህፃናት ህይወት አስጊ እንደሆነው በአገሪቱ ለሚገኙ ህፃናትም ድርቁ በአስጊነቱ በተመሳሳይ ደረጃ የሚገለጽ ነው ብሏል ።
የህፃናት አድን ድርጅቱ ተወካይ ካሮሊን ሚልስ “በአለም ላይ ያሉን የአስቸኳይጊዜ እርዳታ ፈላጊዎች ምድብ ሁለት ናቸው ።ሶሪያ አንደኛዋ ስትሆን ኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ናት።ለአስቸኳዩ ችግር መፍቻ 100 ሚሊዮን ዶላር ያስፈልጋል ብለናል “ማለታቸው ተሰምቷል ።
አልጀዚራ በኢትዮጵያ ስለተከሰተው ድርቅ ያናገረው የአስር ልጆች አባት ሙሐመድ ዱባለ ከድርቁ በፊት 53 ላሞች እንደነበሩት በማስታወስ አሁን የቀሩት አምስት ብቻ መሆናቸውን ይገልጻል ።
ሙሐመድ ለሁለት ጊዜያት ከመንግስት የምግብ እርዳታ ቢያገኝም ከድርቁ ስፋት የተነሳ በቂ አለመሆኑን ይናገራል ።
ሙሐመድ “ለህዝቡና ለልጆቻችን በጣም ሰግቻለሁ ምክንያቱም ዝናብ የለም ።ዝናብ ከሌለ ደግሞ ምግብ ና ወተት ስለማይኖር ሰዎች ይሞታሉ “ብሏል። ( Dawit S. Yemesgen)
