የኦሮሞ ጀግኖች ተቃውሞ በየከተሞች እና በአዲስ አበባ ዙሪያ ቀጥሎ ሱሉልታ ላይ የባህርዳር መንገድ ተዘግቷል::


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


የኦሮሞ ጀግኖች ተቃውሞ በየከተሞች እና በአዲስ አበባ ዙሪያ ቀጥሎ ሱሉልታ ላይ መንገድ ተዘግቷል::
‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎OromoProtests‬ ‪#‎AddisAbabaMasterPlan‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬

የወገኖቹን ደም ለማፍሰስ ወደ ሱሉልታ እየተጠጋ ያለው የአጋዚ ኮማንዶ ጦር።

Minilik Salsawi – የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተቃውሞ እና የሕዝብ ብሶት የወለዳቸው በራሱ በሕዝቡ መሪነት የሚካሄዱ ተቃውሞዎች ቀጥለዋል::በዛሬው እለት እየተደረገ ባለው ተቃውሞ የጎጃም በር በመዘጋቱ ወደ ባህርዳር የሚጓዙ የጭነት መኪኖች ይሁን የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብሶች ከሱሉልታ ሲመለሱ ውለዋል::ሱሉልታ ላይ ሕዝቡ መንገዱን በመዝጋት ተቃውሞውን እያሰማ ይገኛል::

በሱልልታ ከተማ አየር ላይ ከደብረዘይት የተነሱ የታጠቁ ወታደሮችን የጫኑ ሂሊኮፕተሮች በማንዣበብ ላይ ይገኛሉ::በምእራብ ሸዋ ሜታ ሮቢ የፓርላማ ተወዳዳሪ የነበረው የኢላ አሙማ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አስተማሪ ታደሰ ጸጋዬ ከሕወሓት ወታደሮች በተተኮሰ ጥይት መገደሉ ታውቋል::
በሱሉልታ ከተቃውሞው ጋር ግንኙነት ያሌላቸው 200 የወን ሰራተኞች በሕወሕት ወታደሮች ተይዘው ተውስደዋል::ሕዝቡ ተቃውሞውን እንደቀጠለ ነው::በአዲስ አበባ በዳግማዊ ምንሊክ ሆስፒታል በኦሮሚያ ክልል በሕወሓት የተገደሉትን ተማሪዎች ሃዘናቸውን ለመግለጸ የተሰበሰቡ የሆስፒታሉ ዶክተሮች እና ነርሶች በአገዛዙ ፖሊሶች ታፍሰው ተወስደዋል::የስዊዲን መንግስት በኢትዮጵያ የኦሮሚያ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ጉዳይ ላይ የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን የጋራ አቋም እንዲይዝ ጥሪ አቀረበ። ዛሬ በአራዳ ካንጋሮ ፍርድ ቤት በርካታ እስረኞች ያመለጡ ሲሆን ከፍተኛ ቶክስ እንደነበር ተሰምቷል::

ተቃውሞው ቀጥሎ በወለጋ ኦብዲ በምእራብ ሸዋ ሜታ ሮቢ እጅግ ከፍተኛ ተቃውሞ በመሰማት ላይ ይግኛል::እንዲሁም በተለያዩ ዩንቨርስቲዎች ለሊቱን ወያኔ በተለያዩ ብሄሮች መካከል ሊያነሳ ያቀደውን ግጭት የከሸፈበት ሲሆን የኦሮሞን ሕዝብ የሚያንቋሽሹ ጽሁፎች በካምፓሶች ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ለጥፎ ያደረ ቢሆን የሚሰማው አጥቷል::ሕብረተሰቡ ይህ ሊወድቅ የተቃረበውን የበሰበሰ አገዛዝ የከፋፍለህ እና የአጋጭተግ ግዛ ዲስኩሩን እና ተንኮሉን ሳይሰማ ባለን አቅም ሁሉ በጋራ ቆመን በአንድነት ከስልጣን በማባረር ሕዝባዊ መንግስት በመመስረት ሕዝብን የስልጣን ባለቤት ማድረግ ይገባናል::

Minilik Salsawi's photo.