የዞን ዘጠኝ ጦማርያን የልደታ ካንጋሮ ፍርድ ቤት ውሎ ለ32ኛ ጊዜ ለሓምሌ 22 ተቀጠረ::
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
Minilik Salsawi በዛሬው እለት ከእስር ባልተፈቱ አራቱ የዞን ዘጠኝ ጦማርያን ላይ ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ተይዞ የነበረ ሲሆን በቦታው የጦማርያኑ ቤተሰቦች እና ጓደኞቻቸውን ጨምሮ ዲፕሎማቶች እና ጋዜጠኞች በካንጋሮው ፍርድ ቤት ተገኝተዋል::እንዲሁም በቅርቡ የተፈቱት ጋዜጠኞች እና ጦማርያን ርእዮት አለሙን ጨምሮ በፍርድ ቤቱ ታድመዋል::ያልተፈቱት አራቱ ብሎገሮች በፍቃዱ;ናትናኤል:አጥናፍ እና አቤል ከእስር ቤት ሲነሱ በፍርድ ሂደቱ ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ለመግለጽ ጥቁር ካኒተራ ቢለብሱም ወደ ፍርድ ቤቱ ከመንቀሳቀሳቸው በፊት በሃይል እንዲቀይሩ እንደተደረገ ተሰምቷል::የካንጋሮው ችሎት በመሙላቱ እጅግ በርካታ ሰዎች ፍርድ ቤቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ተቀምጠው የችሎቱን ውሳኔ ሲከታተሉ ነበር::
በዛሬውም ችሎት የዳኞች ማርፈድ የተለምደ ነው::አቃቢ ሕጎች በቦታው አልደረሱም:: የችሎት አስተባባሪዋ አቃቤ ህጎች ተደውሎላቸዋል ይመጣሉ::በማለት ስትናገር ተደምጧል::ፋይሉ በፍርድ ቤቱ ጠረጴዛ ላይ ቀርቦ ዳኞቹ በማርፈዳቸው የሚያየው አጥቶ ነበር::አቃቢ ሕጎች ከፍርድ ቤቱ በተደጋጋሚ ተደውሎላቸው በቦታው ደርሰው ከካንጋሮው ፍርድ ቤት ተዋህደዋል::ዳኞች በቦታቸው ተሰይመው የምስክሮች ቃል በፅሁፍ አልተገለበጠም በሚል ሰበብ ለሰላሳ ሁለተኛ ጊዜ ለሃምሌ 22 ሲቀጠር ጦማሪ አጥናፍ ” ዛሬ ከታሰርን 450 ኛ ቀናችን ነው በቀጠሮዎች መራዘም ምክንያት ቤተሰቦቻችን እና ወዳጆቻችን እየተንገላቱ ስለሆነ ፍርድቤቱ ይሄንን ከግምት ያስገባልን። ” ሲል ለፍርድ ቤቱ ተናግርዋል::«ለ450 ቀን ያህል በእስር ቆይተናል። በመሆኑም አጭር ቀጠሮ በመስጠት ለብይን ልንቀጠር ይገባል» አጥናፍ ብርሃኔ ሲል «አጠር ያለ የ10 ቀን ቀጠሮ እንስጣችሁ» በማለት ዳኛው መልሶለታል::