ባለፉት ስድስት ወራት 89 የአማራ ክልል ዳኞች በደኅንነት ስጋት ስራ ለቀዋል

የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ባለፉት ስድስት ወራት 89 የክልሉ ዳኞች በደኅንነት ስጋትና በክፍያ ማነስ ሳቢያ ሥራ መልቀቃቸውን ለክልሉ ምክር ቤት ባቀረበው ሪፖርት አስታውቋል።

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ፣ በክልሉ በሚካሄደው ግጭት ሳቢያ 28 የወረዳ ፍርድ ቤቶች ምድብ ችሎቶች ባኹኑ ወቅት አገልግሎት እየሠጡ እንዳልኾነ ተናግሯል።

የክልሉ ጸጥታ አካላት ባንዳንድ አካባቢዎች ዳኞች ከሚሠጧቸው ወሳኔዎች ጋር በተያያዘ ዳኞችን እንደሚያስሩ የገለጠው ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ፣ የክልሉ ምክር ቤት ችግሩን ለመቅረፍ ማስተካከያ እንዲደረግበት እንዲያደርግ ጠይቋል