ብልፅግና አየር ሃይሉን ከተቆጣጠረ ጀምሮ የአየር ሃይልን ፕሮፌሽን ምን ያክል እንደገደሉት መቀመቅ እንደከተቱት ተጨባጭ መረጃዎች ያሳያሉ

ብልፅግና አየር ሃይሉን ከተቆጣጠረ ጀምሮ ከሞተበት አስነሳሁት እንደሚለው ሳይሆን እነ ብርሃኑ ጁላና ይልማ መርዳሳ አየር ሃይሉን በባሰ ሁኔታ ምን ያክል መቀመቅ እንደከተቱትና በዘርና በፒለቲካ አድሏዊነት የአየር ሃይልን ፕሮፌሽን ምን ያክል እንደገደሉት የሚከተሉት በሰባት አመት ውስጥ የተከሰቱ ተጨባጭ መረጃዎች ያሳያሉ ከነዚህም ውስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል

1 – አየር ሃይሉን በፍፁም ዘረኝነትና ወገንተኝነት በማዋቀር በርካታ የተቋሙን የአማራና የትግራይ ተወላጅ አመራሮችንና ፓይለቶችን በማግለል በማሳደድና ከዛም አልፎ ለእስርና ስደት በመዳረግ ሃገሪቱ ከፍተኛ ሪሶርስ በማውጣት የአሰለጠነቻቸውን ከ መቶ በላይ ( ስማቸውን መዘርዘር ይቻላል ) ብርቅየ አብራሪዎች በዘርና በፒለቲካ አስተሳሰብ ሃገራቸውንና ተቋማቸውን እንዳይጠቅሙ ተደርገዋል የዚህም ውጤት ማሳያው ዛሬ በርካታ የበረራ ስኳድሮኖች ሲኔር ፓይለቶቻቸውንና አመራሮቻቸውን አጥተው ከፍተኛ ዶላር ወጭ ተደርጎ በውጭ መርሰነሪ ፓይለቶች ተተክተዋል ለምሳሌ አሁን ላይ ብልፅግና የሚኮፈስበትና ፕሮፓጋንዳ እየሰራበት ያለው ኤር ሾው ላይ የተሳተፉት በሙሉ በሚባል ደረጃ የውጭ መርሰነሪ ፓይለቶች ናቸው
ለምሳሌ su -27 – Russian retired pilots
Yak-130 Russian retired pilots
Grob -120 Paraguay & Argentina
L-39 – check Republic pilots
ሲሆኑ በተለይም L-39 አድቫንስድ ጀት ማሰልጠኛና su 27 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ሁኔታ በውጭ አስተማሪዎች ተተክተዋል ። ይሄም የብልፅግና ዘረኝነትና ብሔርተኝነት ምን ያክል ፕሮፌሽንኑን እየጎዳው እንዳለ ያሳያል ።

2- ከሰሞኑ በብልፅግና የሚዲያ ሰራዊት ብዙ ሲወራና በ ፋና በኢቢሲ ብዙ ሲነገርለት የነበረው አጠቃላይ ራሻን ጨምሮ አምስት ሃገራት በዚህ ኤርሾው ላይ ይሳተፋሉ ተብሎ ቢጠበቅም በሃገሩና በጎረቤት ሃገራት ጠብ አጫሪ የሆነ መንግስት የሚያሳየው ኤርሾው ላይ አንሳተፍም በማለት ከ UAE በስተቀር ሁሉም ሃገሮች ቀርተዋል ( ይሄን ከቀረቡ የመንግስት ዜናዎች ጋር ማስተያየት ይቻላል ሃገሮቹ ለምን ቀሩ ? እንዴት ? ብዙ ጥያቄ የሚያስነሳና የብልፅግናውን አየር ሃይል ውድቀት የሚያሳይ ነው )
3- ሌላኛው ተቋሙን ምን ያክል መቀመቅ ውስጥ እንደከተቱ ማሳያ የሚሆነው ብልፅግና አየር ሃይሉን ከያዘው በኋላ አየር ሃይሉ በታሪክ ሰርቶት በማያቀው የሴፍቲና የፕሮፌሽናሊቲ ጥሰት ምክኒያት ሙሉ ለሙሉ ከማንኛውም ሰላም ማስከበር ተልእኮ መውጣቱ ነው ፡ በጣም የሚገርመው ይልማ መርዳሳ ከመጣ ጀምሮ ተቋሙ ከማንኛውም አለም አቀፍ ተልእኮ ተባሯል ፡ ይሄም በዘር የተቧደነ ቡድን ፕሮፌሽኑን እንደገደለው ማሳያ ነው ። በተዋጊም በትራንስፖርትም ንቁ ተሳታፊ የነበረው ተቋም በዚህ ሰባት አመት ውስጥ አንድ እንኳን ተሳትፎ ማድረግ ተስኖታል ። ከዚህ በላይ ተቋም መግደል ምን አለ ?

4- በዚህ ሰባት አመት ውስጥ አየር ሃይሉ በታሪክ ውስጥ አድርጎት በማያቀው እጅግ በተጋነነ ሁኔታ የራስ ወገንን የመጨፍጨፍ ግፍ ፈፅሟል ይሄም ተቋሙ ከህዝብ ጋር የተራራቀበትና የተለያይየበት ዘመን ነው ፡ በዚህም በአማራ ክልል ብቻ 78 የድሮን 62 የጀትና የሄሊኮፕተር ቦምብ ድብደባ ተፈፅሟል ይሄ የትኛውም የጥላት ሃገር ላይ ራሱ ሊፈፀም የማይችልና አየር ሃይሉ በታሪኩ አድርጎት የማያቀው ነው ።

5- ይሄኛው ትንሽ አስደጋጭ ይመስላል ግን ነጭ እውነት ነው በተለያየ ጊዜ በስህተት የሚደረጉ የቦንብ ድብደባዎች በማስመሰል የአማራ ብልፅግና አድማ ብተናንና ሚሊሻዎችን በጅምላ በቦምብ መጨረስ ተደጋጋሚ እየተስተዋለ ያለ ነገር ነው ። ሚዲያዎች ከሰሞኑ በዋግህምራ ሚኒሻዎች ላይ የተፈፀሙ ድብደባዎችን ብቻ ቢዘግቡም በምስራቅ ጎጃም በአባይ በረሃ በ ጎንደር ዕብናት አካባቢ የአማራ አድማ ብተናንና ሚሊሻዎችን ስህተት ነው በሚል በቦምብ የምጨረስ አሳዛኝ ሴራ ተሰርቷል ።

6- በጠቃላይ ተጨባጭ መረጃዎች እንደሚታሳዩት ስኳድሮኖችና ክንፎች 27 አመት በኢሃዲግ ሙቷል እንደተባለው ሳይሆን አሁን ላይ በባሰ ሁኔታ መቀበሩን ያሳያል ለምሳሌ
ኢንተርሴፕተር ክንፍ( interceptor wing) 18 su 27ቶች ነበሩት ብልፅግና ከያዛቸው በኋላ ያሉት ስድስት ብቻ ናቸው
ብልፅግና ከመጣ በኋላ ቦምበር ክንፍ ሙሉ ለሙሉ ተዘግቷል ምክኒያቱም ፓይለቶቹ ሙሉ ለሙሉ በዘረኝነት ከፕሮፌሽናቸው እንዲገለሉ ተደርገዋል ታስረዋል ለስደት ተዳርገዋል ( ከነዚህም ውስጥ ጄኔራል አለማየሁ ፡ ኮል ዳግሞ ወርቃፈራው ፥ ሻ/ቃ ይሁን ሲሳይ ፥ ሻ/ቃ ታደሰ አብርሃ፥ ሻ/ቃ አብዱ ረህማን ፥ ሻ/ቃ ሳሙኤል አስራት ፥ ሻ/ቃ አንድ አምላክ ወዘተ ይገኙበታል ) ። ሌላው ብልፅግና ከመጣ በኋላ 100% ሙሉ ለሙሉ የተዘጋ ክንፍ ደግሞ ተዋጊ ሂሊኮፕተር ክንፍ ሲሆን ይሄም በተመሳሳይ ሲኒየር ፓይለቶቹን በዘረኝነት በማሰርና በማሳደድ ለስደት በመዳረግ ነው ( ስማቸውን መዘርዘር ይቻላል እንዳጠቃላይ በዚህ 7 አመት 30 የተዋጊ ሂሊኮፕተር ሲኒየር ፓይለቶች በዘረኝነት ከጥቅም ውጭ ተደርገዋል):….

ብልፅግና በ2030 ከአፍሪካ አንደኛ አደርገዋለሁ የሚለው አየር ሃይል ምናልባት አንደኝነቱ ከመጨረሻዎቹ ይሆን ?