በ47 ቀን 12 ሾፌር 6 ተሳፋሪ በጥይት ተገድለዋል።
ከ05/01/2018 እስከ 21/02/2018 ዓም ድረስ ባለው የ46 ቀን ጊዜ በሀገሪቱ በተለያዩ ክልሎች 12 ሾፌር እና 6 ተሳፋሪዎች ተገድለዋል። ይህ ለገፃችን የደረሰ ብቻ ነው ለእኛ ያልደረሱን ግድያዎች ይኖራሉ። ከግድያ በተጨማሪ በዚሁ ጊዜ ለቁጥር የሚታክቱ እገታዎች ተፈፅመዋል።

በሀገሪቱ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ብዛት ያላቸው አሽከርካሪዎች ረዳቶች እና ተሳፋሪዎች በጉዞ ላይ እያሉ እየታገቱ ለፍተው ያፈሩትን ከፍለው የሚለቀቁ ነፍሳቸውን በወንበዴ ጥይት በግፍ የሚነጠቁ ሆነዋል።
አሽከርካሪዎች አፈና ግድያ እና ዝርፊያ እየተፈፀመባቸው ቢሆንም ይህንን ችግር ሚዲያዎች በዝምታ የሚመለከቱት የሰባዊ መብት ተሟጋች ነን የሚሉ በችግሩ ጥልቀት ልክ የማያወግዙት። መንግስት ችግሩን ለመፍታት በጉዳቱ ልክ ተገቢ ስራን ያልሰራበት። ብዛት ያለው ቤተሰብ ያለ አስተዳዳሪ የቀረበት ልጆች ጎዳና ለመውጣት የተዳረጉበት ጭካኔ የተሞላበት ተግባር ሁሉም ሊቃወመው ይገባል።
በምስሉ የሚታዩት በዘራፊ ወንበዴዎች በግፍ በጥይት ከተገደሉት ውስጥ ያሉ ናቸው ነፍስ ይማርየሚዲያ ባለሙያዎች እንዲህ ያሉ የግፍ ግድያዎችን በጉዳቱ ስፋት ልክ የማይዘግቡበት ድምፅ ሆነው ችግሩን ለማሳየት የማይጥሩበት ሁኔታ የሚያሳዝን የሚያሳፍት ከሰባዊነት ቦታ የራቁ ለዜጎች ሞት የማይጨነቁ ከሙያው ስነ ምግባር የራቁ መሆናቸውን ያየንበት ነው።
መንግስት በችግሩ ጥልቀት ልክ ሊሰራ ይገባል ችግር በሚፈፀምባቸው አካባቢዎች ያሉ ነዋሪዎች ድርጊቶችን ሊያዎግዙ ዘራፊ ነፍስ ቀጣፊ የሆኑ ግለሰቦችን ሊቃወሙ ይገባል።
ፍትህ በግፍ ለሚገደሉ።