የሀገራችን ኢኮኖሚ ስርዐት ድሃው ማህበረሰብ ሰርቶና በልቶ እንዲያድር ፍትሐዊ እንዲሆን እንጸልይ፡፡

ሀገራዊ የጾም ፀሎት ጥሪ ከመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን !

መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ከየካቲት 1 እስከ የካቲት 15 ድረስ የሚዘልቅ ሀገራዊ የጾም ፀሎት አውጃለች።

ቤተክርስቲያኗ በልመና / ምልጃ ጸሎት ወቅት ፦

➡️ ” በሀገሪቱ በተለያዩ ሥፍራዎች ያሉ የፖለቲካ ኃይሎች በኃላፊነት መንፈስ በጋራ ለሀገር እና ለህዝብ በአንድነት መስራት የሚችሉበትን ጥበብ፤ እውቀትና ማስተዋል እግዚአብሔር እንዲሰጣቸው እንለምን። “

➡️ ” በሀገራችን በሚገኙት የኦሮሚያ፤ የአማራ እና የትግራይ ክልሎች ያለው አፍተኛ የጸጥታ ችግር ጌታ እንዲያቆመው እንጸልይ። “

➡️ ” በምድሪቱ ላይ ፍትህ እንዲሰፍን እንዲሁም በተለያዩ የሥልጣን ደረጃዎች ያሉ የመንግስት አካላት ሕዝቡን በከፍተኛ ኃላፊነት፤ አክብሮትና ቅንነት ማገልገል የሚችሉበትን ጥበብ፣ ማስተዋልና የልብ ስፋት እግዚአብሔር እንዲሰጣቸው እንለምን። “

➡️ ” የሀገራችን ኢኮኖሚ ስርዐት ድሃው ማህበረሰብ ሰርቶና በልቶ እንዲያድር ፍትሐዊ እንዲሆን እንጸልይ፡፡ “

… ብላለች።