” ታዳጊዎቹ በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ነው ሞተው የተገኙት። ፖሊስ ምርመራ እያደረገ ነው ” – በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያዊያን ተወካይ

” ታዳጊዎቹ በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ነው ሞተው የተገኙት። ፖሊስ ምርመራ እያደረገ ነው ” – በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያዊያን ተወካይ

ነዋሪነታቸዉን በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ከተማ ያደረጉ ዲቦራ መንግስቴ እና ኦፕራ መንግስቴ የተባሉ ሁለት እህታማማቾች በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ሞተው መገኘታቸውን ‎በደቡብ ኢትዮጵያ የኢትዮጵያዊያን ማህበረሰብ ተወካይ ኮሚቴዎች መካከል አቶ ዓለማየሁ ቲጁማ አሳውቀዋል።

‎በሁለቱ እህትማማቾች አሟሟት ዙሪያ ፖሊስ ምርመራ እያደረገ መሆኑን ያነሱት አቶ ዓለማየሁ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ” በካምፓስ /ዩኒቨርሲቲ/ውስጥ ሞተው ተገኙ ” በሚል የተሰራጩ መረጃዎች የተሳሳቱና ከእውነታዉ የራቁ ናቸው ብለዋል።

‎አስክሬናቸው በደቡብ አፍሪካ ሕዝባዊ ሽኝት ተደርጎ ነገ ዐርብ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚላክም ገልፀዋል።