በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች በአዲስ አበባ ውስጥ ወጣቶች እየታፈኑ ነው ሲል ኢዜማ ብልፅግናን ከሰሰ

ኢዜማ የመንግስት አካላት በሚል በጠራቸው የፀጥታ ኃይሎች በአዲስ አበባ ውስጥ ወጣቶች እየታፈኑ እና የት እንዳሉ ማወቅ አሰቸጋሪ እየሆነ እንደመጣ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አሳውቋል፡፡

ባለፉት ጥቂት ቀናት በአዲስ አበባ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ወጣቶች በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እየታፈኑ የት እንደገቡ ሳይታወቅ መሰወራቸውን ከቤተሰቦቻቸው እና ከተለያዩ አካላት ለመገንዘብ ችያለሁ ብሏል ኢዜማ፡፡

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ዛሬ በሕግ መጠየቅ ያለበት የትኛውም ዜጋ በሕግ ሊጠየቅ የሚገባው ሕጋዊ በሆነ መንገድ ብቻ ነው በሚል ዛሬ ሰፊ መግለጫ አስነብቧል፡፡

ባለፉት ጥቂት ቀናት በአዲስ አበባ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ወጣቶች ኢዜማ የመንግስት አካላት የፀጥታ ኃይሎች እየታፈኑ የት እንደገቡ ሳይታወቅ መሰወራቸውን ከቤተሰቦቻቸው እና ከተለያዩ አካላት ለመገንዘብ መቻሉን በመግለጫው አትቷል፡፡

ይኽን የመንግሥት ተግባር ይበልጥ አስከፊ የሚያደርገው እነዚህ ታፍነው የተወሰዱ ወጣቶች የት እንደሚገኙ አለመታወቅና ቤተሰቦቻቸውም በመንግሥት አካል የተያዘ ግለሰብ ሊገኙባቸው ይችላሉ የሚሏቸውን ቦታዎች ቢያስሱም ለማግኘት አለመቻላቸው ነው ሲል ገልጻል።

ይህ ብቻ አይደለም አንዳንዶቹ ከተወሰኑ ቀናት መሰወር በኋላ በድንገት የት እንደነበሩ እንኳ መናገር በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ሆነው ወደቤታቸው መመለሳቸው ማወቅ ችያለሁ ብሏል፡፡

አሁንም በዚህ አይነት አፈና ውስጥ ያሉ ወጣቶች እንዳሉ ፓርቲያችን አረጋግጧል ካለ በኃላ ቤተሰቦቻቸውም በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ እንደሚገኙ ገልጸል፡፡