“በደብረ ማርቆስ ከተማ 670 መምህራን ታፈኑ”
206ኛ ኮር በመማማር ማስተማር ሒደቱ ከመምሕራን ጋር ለመዋያየት ባደረገው ጥሪ መሰረት ከደብረ ማርቆስ ከተማ ተነስተው ወደ ስብሰባ ሲሔዱ የነበሩ 670 መምህራን እና ዕርሰ መምህራን በአገዛዙ ሰራዊት ታፍነዋል።
ከ25 በላይ መኪና በማዘጋጀት ከ206ኛ ኮር አመራሮች ጋር ለመወያየት ያቀኑት 670 መምህራን ከህዳር ወር ጀምሮ የሁለት ወር ደሞዝ በአምባገነኑ ስርዓት ተነጥቀዋል። ትግሉን በማጠልሸት ተጠምዶ የነበረው የምስራቅ ጎጃም ካድሬ ትናንት ጥር 03/2018 ዓ/ም ከጠዋት ጀምሮ ኬላ ዘርግቶ መምህራንን በማጎር የተጠመደ ሲሆን ከ74 በላይ መምህራን በከፍተኛ ድብደባ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተረጋግጧል።