ከወረታ ደብረታቦር ባለው አውራ ጎዳና በአገዛዙ ተደራጅተው በፋኖ ስም ሲዘርፉ የነበሩ ባንዳዎች ላይ ጥብቅ እርምጃ መወሰዱ ተነገረ!

ከወረታ ደብረታቦር ባለው አውራ ጎዳና በአገዛዙ ተደራጅተው በፋኖ ስም ሲዘርፉ የነበሩ ባንዳዎች ላይ ጥብቅ እርምጃ መወሰዱ ተነገረ!

በአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ኮር ስር ከነበልባሉ ፎገራ ክ/ጦር የተወጣጡ የፋኖ አሃዶች በወረታ እና በደብረታቦር መካከል ሀገረ ሰላም፣ አርባ አምባ፣ በቆሽ በርና ውር ተብለው በሚጠሩ አከባቢዎች ላይ በወሰዱት እርምጃ በርካታ ባንዳዎችን ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ቀጠናውን ማፅዳታቸውን መረብ ሚዲያ ከክፍለጦሩ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ለማረጋገጥ ችሏል።

ፋኖ፡ አገዛዙ የአማራ ሕዝብን በማሕበራዊና በኢኮንሚያዊ ሕይወቱ እረፍት እንዲነሱለት አደራጅቶ ያሰማራቸው ዘራፊ ወንበዴዎች ላይ የሚወስደውን ጥብቅ እርምጃ አጠናክሮ ቀጥሏል።