በውጫሌ ዙሪያ በተደረገ ተጋድሎ በልጅ እያሱ ኮር 24ኛ ክፍለ ጦር ድል አስመዘገበች!
ልጅ እያሱ ኮር 24ኛ ክፍለ ጦር የአምባሰል ወረዳ መቀመጫ በሆነችው ውጫሌ ከተማ ዙሪያ ዛሬ ታህሳስ 9/2018 ዓ.ም ንጋት 12:00 ጀምሮ ወደ ጠላት ምሽግ ዘልቀው በመግባት ባደረጉት ከባድ ተጋድሎ እስከ ቦምብ ጭምር በመጫበጥ በርካታ የጠላት ሃይል ደምስሰውና አቁስለው ታላቅ ጀብድ ፈፅመው ድል አስመዝግበዋል::
24ኛ ክፍለጦር በተጋድሎው ውጫሌ ከተማ ቁንጥሮ ላይ የጠላትን ምሽግ ሁሉ ደምስሰው በመግባት ትልቅ ጀብድ የፈፀሙ ሲሆን ከ40 በላይ የጠላት ሃይል ሙትና ቁስለኛ አድርገው ለጊዜው ቁጥሩ ያልታወቀ የነፍስ ወከፍ ክላሽና የተለያዩ ተተኳሾችንም ማርከዋል::
የፋሽስቱ ብልፅግና ሰራዊት ከተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢ እና ከኦሮሞ ብልፅግና ልዩ ሃይል ጭምር ታፍሶ ሲመጣ በምድር በመካናይዝድና በአየር ሃይል ጄትና ድሮን ከፍተኛ ድጋፍ ሊደረግለት ቃል ተገብቶለት መጥቶ ውጊያ እያደረገ ያለ ሲሆን አየር ንብረቱ ለድሮን በማይመችበት በዳመና ጊዜ ወኔው ተሰልቦና ውጊያ ከብዶት በጅምላ እየተደመሰሰ እና እየተማረከ ይገኛል::