አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ መግለጫ

 

አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና
በላይ ዘለቀ ዕዝ

ጀግናው ሰራዊታችን ሀምሌ 11/2017 ዓ.ም የአገዛዙን ሰራዊት የሚደመስስ የረቀቀ ወታደራዊ ዕቅድ በማቀድ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ በመተማ ወረዳ ሽመለ ጋራ፣ደለሎ ቁጥር አንድና ቁጥር አምስት በከፈተው ወታደራዊ ማጥቃት ከ170 በላይ የተደመሰሰ፣ከ40 ጠላት እጅ ሰቶ ተማርኳል፣ከ100 በላይ የነፍስ ወከፍ የጦር መሳሪያ ሲማረክ 06 የቡድን የጦር መሳሪያ ብሬንና ስናይፐር ተማረኳል።
አንድ ዲሽቃ ሞተራይዝድ የተማረከ ሲሆን 05 አይኮም ወታደራዊ ሬድዮን ጨምሮ 01 ሽጉጥ የተማረከበት ስኬታማው ኦፕሬሽን ነው።
ዘግይቶ በደረሰን መረጃ መሰረት ደጃዝማች 4ኛ ኮርና ከመይሳው ካሳ 2ኛ ኮር አጣናው ዋሴ ክ/ጦር በቅንጅት የብርሃኑ ጁላ ታጣቂን በበርሃማው ጠረፋማ ቀጠና አንጀቱን በጎተቱበት ውጊያ የጠላት 78ኛ ክ/ጦር 1ኛ ሬጅመንት ሙሉ በሙሉ ሲደመሰስ 2ኛ ሬጅመንትም በከፊል ተደምስሳለች።

የዓብይ አህመድ 78ኛ ክ/ጦር 1ኛ ሬጅመንት አዛዥ ሻለቃ ኤፍሬምም በደለሎ ቁጥር አንድ ከተደመሰሱት መካከል እንደሚገኝበት ማረጋገጥ ተችሏል።

ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ በላይ ዘለቀ ዕዝ

ዮሐንስ ንጉሱ ሙጨ

Amhara Fano National Force
@AmharaFanoNF