Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Ejersa
Member
Posts: 3976
Joined: 05 Nov 2019, 10:39

የወያኔ ፌዴራሊዝም ትልቋን ኢትዮጵያ የምትባለዋን ዶሮ አንስተህ ፉርኖ ውስጥ አስገብተህ ቀልታ ስትወጣ የሚጣፍጠውን እኔ እበላለሁ፤ ሌላህ ግን ልፋጭ ብላ ያለ ስርዓት ነው

Post by Ejersa » 07 Nov 2019, 19:29

የወያኔ ፌዴራሊዝም ትልቋን ኢትዮጵያ የምትባለዋን ዶሮ አንስተህ ፉርኖ ውስጥ አስገብተህ ቀልታ ስትወጣ የሚጣፍጠውን እኔ እበላለሁ፤ ሌላህ ግን ልፋጭ ብላ ያለ ስርዓት ነው፡፡ ስም ሰጡት ግን Modern ስም ፌዴራሊዝም አሉት፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ግን ፌዴራሊዝም አልነበረም፤ ከአሁን ወዲያ ነው ፌዴራሊዝም መገንባት የምንችለው፡፡ የሚገርምሽ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን የሚል ሌላ ነገር አስቀመጡ አጠገቡ፤ እርሱ ቁጭ ብሎ ሌላው አማራውም የሀገር ልብሱን፣ አፋሩም የሀገር ልብሱን፣ ሶማሌውም ደቡቡም ኦሮሞውም የሀገር ልብሱን ለብሶ ይጨፍርለታል እርሱ እንደፈረንጅ colonialist ቁጭ ብሎ ይመለከታል (ይዝናናል)፡፡ፕ/ር መሀመድ ሐሰን የሶማሌ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አማካሪ