በኢትዮጵያ የጎሳ ፌዴሬሽን መፍጠር አይቻልም
በጎሳ ፌዴሬሽን ወስጥ መተማመን በፍጹም ሊኖር አይችልም። በኢትዮጵያ ውስጥ ፌዴሬሽን የሚለው ቃልና ጽንሰ ሃሳብ ምናልባት ከ60 አመታት በላይ እድሜ አለው፤ ከኤርትራ ፌዴሬሽን እንኳ ብንጀርምር። በአሁን ሰአት በየቀኑ ይህን ቃል ሳንሰማ አንውልም። ነገር ግን አንድም ቦታ ስለዚህ ቃል ሆነ ስንጸ ሃሳብ እውነተኛ ትርጉም ሲጠቀስ ስምቼ አላውቅም ።
ፌዴሬሽን ምን ማለት ነው? የቃሉ ስረ ምንጭስ ምንድን ነው? ለመሆኑ የጎሳ ፌዴሬሽን በእውን በተግባር ሊኖር ይችላልን?
ፈደረ ማለት አመነ ማለት ነው፤ ማለትም ፈደርነት እምነት፣ ኪዳን፣ ማመን፣ አንድን ነገር እንደ እውነት መቀበል፣ አንድን ነገር ማተለቅ፣ ማግነን፣ ማክበር ማለት ነው። ሰው ከአምላኩ ጋር ያለው አንድነት በኪዳን፣ በፈደር፣ በእምነት ላይ የተመሰረተ ነው። ማህበርተኞች እቁብ የሚጠጡት በፈደር፣ በእምነት ላይ ተመስርተው ነው። ስለዚህ ያለ እምነት፣ ያለ መተማመን ፌዴሬሽን የሚባል ጽንስ፣ ልምድም ሆነ ንድፈ ሃሳብ በአለም የለም።
ስለሆነም በአላማ፣ በቁጥር፣ በባህል፣ በራእይ ሆነ በፍላጎት የተለያዩ ብቻ ሳይሆን የሚጠርጠሩ፣የሚፎካከሩ፣ የሚጣሉ ጎሳዎች በእምነት፣ በኪዳን በመተማመን ቃል ኪዳን ላይ የተመሰረተ ህብረትም ሆነ መንግስት ሊያቆሙ አይችሉም። ራሱ የፌዴራላዊ ህብረትም ሆነ የጋራ መንግስት ሊያቆሙ የሚችሉት በፈጣሪም ሆነ በሕግ ፊት እኩል የሆኑት የኢትዮጵያ ግለሰቦች ናቸው። በኢትዮጵያ ውስጥ የተፈለገው አይነት ፌዴራሊዝም ሊቆም ሊጽና የሚችለው በኢትዮጵያ ዜጋዎችና በዜጋ ፍልስፍና፣ በዜጋ ፖለቲካ ንድፈ ሃሳብ እና በዜኘት ካልቸር ላይ ነው።
-
- Senior Member+
- Posts: 30911
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ
..……………………………………………………………………………...
-
- Senior Member+
- Posts: 30911
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ
ይህን ራሱን ያስተማረ ድንቅ ምሁር ከዳር እስከ ዳር ስሙት !!! በዚህ ሃረግ ከላይ ያነሳትህን ችግር እምርቱ ላይ እሳየን ነው
-
- Senior Member+
- Posts: 30911
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ
የጠ/ሚ አቢይ የከፋ ውሎ ሙሉውን ተከታትዪዋለሁ ! የከፋ ህዝብ ስልጡንነትና መረጋጋት እጅግ ደስ ይላል !! ያዲሱ ካልቸር ምልክት !!
-
- Senior Member+
- Posts: 30911
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ
..……………………………………………………………………...
-
- Senior Member+
- Posts: 30911
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ
ዛሬ 2020 አ/ም ነው ። ይህን ነገር የጻፍኩት የዛሬ 25 አመት አካባቢ ነው ። ይዛሬን ያቢይ ያፓርላማ ው ሎ ስከሰማሁ በኋላ አሁንም እንድታነቡት ወደ ላይ ስቤዋለሁ
-
- Senior Member+
- Posts: 30911
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ
እዚህ አስተያየት ውስጥ ለማለት እንደ ሞከርኩት የጎሳ ርዕዮትና የጎሳ ፖለቲካን ወደ ትክክለኛ አቅሙ ለማውረድ እና ዘረኘትን ከፖለቲካ መድረክ ለማውረድ የኢትዮጵያ ሕዝብ እያንዳንዱ በመስኩ ቆራጥ ትግል ማንሳት ግድ ይለዋል ። እንሱም በእምነት፣ በካልቸር፣ በቋንቋ፣ በንግድ፣ በፊሎሶፊ፣ በሙዚቃ ፣ቲያትር ወዘተ: ወዘተ
-
- Senior Member+
- Posts: 30911
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ
እኔ እንደ ዛሬም ደስ ብሎኝ አያውቅም ። የዚህ ሃረግ ትችት የጻፍኩት በሴጵቴምበር 2፣ 1995 (በፈረንጅ) ነበር ። ከ24 አመት በኋላ ያነሳሁት ችግር እንዳለ ስለነበር ከ8 ወር በፊት እዚህ ላይ ፖስት አደረጉት ። አሁን የት/ት ካሪኩለም ማሻሻያ ተደርጎ የሚከተለውን ሰማሁ ። ይህ ትልቅ ዜና ነው። አገራችህን ተስፋ አላት ። ኬር !!!
viewtopic.php?f=2&t=211630
viewtopic.php?f=2&t=211630