What is next? The Abiy Gov't is constantly cruising from one crisis to the next. He is demolishing historic Addis Ababa, he is bombing the Amhara people with impunity, he is secretly plotting to ignite war with Eritrea, he is desperately trying to woo TPLF to be a partner to his destructive agenda, he is interfering with the internal affairs of Somalia and progressively inching towards another war. This man has to be stopped!!
ፑንትላንድ እና ሶማሊላንድ የኢትዮጵያን ቆንስላ ጽህፈት ቤቶችን እንደማይዘጉ አስታወቁ
የሶማሊያ ፌደራል መንግሥት በፑንትላንድ ዋና ከተማ ጋሮዌ እና በሶማሊላንድ ሐርጌሳ የሚገኙት የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤቶችን እንዲዘጉ ያስተላለፈውን ትዕዛዝ እንደማይቀበሉት ሁለቱ ግዛቶች አስታወቁ።
የሶማሊያ ማዕከላዊ መንግሥት የኢትዮጵያ መንግሥት በውስጥ ጉዳዬ ጣልቃ እየገባ ነው በሚል በሞቃዲሾ የኢትዮጵያ አምባሳደር አገሪቱን ለቀው እንዲወጡ እና በከፊል ራስገዟ ፑንትላንድ እና ነጻነቷን ባወጀችው ሶማሊላንድ ያሉት የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤቶች እንዲዘጉ አዟል።
የፑንትላንድ ሶማሊያ መንግሥት በሚለው ይፋዊ መጠሪያዋ የምትታወቀው የፑንትላንድ አስተዳዳር ዓርብ መጋቢት 27/2016 ዓ.ም. ባወጠው መግለጫ ቆንስላው እንዲዘጋ የተላለፈው ትዕዛዝ የሶማሊያን ሕገ-መንግሥትን የሚጥስ ነው በማለት ተግባራዊ እንደማይደረግ አስታውቋል።
ከሶማሊያ በመለየት ነጻ አገርነቷን ካወጀች ሦስት አስርት ዓመታት የሆናት ሶማሊላንድ በበኩሏ በሶማሊያ ፌደራል መንግሥት በኩል በኢትዮጵያ ላይ የተወሰደው ዲፕሎማሲያዊ እርምጃ በሁለቱ ወገኖች በኩል ባለው ግንኙነት ላይ ውጤት የለውም ብላለች።
የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር ሩዳ ጃማ ለቢቢሲ ሶማሊኛ፣ በኢትዮጵያ እና በሶማሊላንድ መካከል ያለው ግንኙነት የሁለቱ አገራት ጉዳይ እንደሆነ እና እየተጠናከረ መሆኑን ገልጸዋል።
“ኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ መልካም ግንኙነት ያላቸው ሁለት አገራት ናቸው” በማለት በሶማሊያ ፌደራል መንግሥት የተወሰደው እርምጃ እንደማያሳስባቸው ተናግረዋል።
ከጎረቤት አገር ኢትዮጵያ፣ ነጻ አገር ነኝ ከምትለው ሶማሊላንድ እና በከፊል ራስ ገዝ ከሆነችው ፑንትላንድ ጋር ፖለቲካዊ እሰጣ ገባው ውስጥ የገባው የሶማሊያ ፌደራል መንግሥት ሐሙስ ሦስቱን መንግሥታት የተመለከተ ጠንካራ ዲፕማሲያዊ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል።
የፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሙሐመድ አስተዳደር የኢትዮጵያው አምባሳደር ሙክታር ከድር ዋሬ በ72 ሰዓታት ከአገር እንዲወጡ ትዕዛዝ ከማስተላለፉ በተጨማሪ አዲስ አበባ በሐርጌሳ እና ጋሮዌ ያላት ቆንስላዎች በአንድ ሳምንት ውስጥ እንዲዘጉ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ይሁን እንጂ የሶማሊላንድ እና ፑንትላንድ በሚኒስትር ደረጃ ያሉ መሪዎች የፌደራል መንግሥቱ ውሳኔን እንደማይቀበሉ ተናግረው ነበር።
ከዚህ በተጨማሪም የሶማሊያ መንግሥት በአዲስ አበባ የሚገኙትን አምባሳደሩን “ለአጠቃላይ ምክክር” ከኢትዮጵያ ለቀው እንዲወጡ ማዘዙን የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሚኒስቴር ይፋ አድርጓል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/c720py2454wo