Please wait, video is loading...
-
- Senior Member
- Posts: 12593
- Joined: 27 Jan 2007, 16:30
- Location: Kaliti
- Contact:
-
- Member
- Posts: 3976
- Joined: 05 Nov 2019, 10:39
-
- Senior Member
- Posts: 12593
- Joined: 27 Jan 2007, 16:30
- Location: Kaliti
- Contact:
Re: ሰበር ዜና : በትግራይ ወጣቶች ሲረሸኑ በለው በለው አንድ ጥይት ይበቃል ሲል የነበረው ተማረከ
Dimtsi Weyane አማርኛ
13h ·
በማህበረ ዴጎ የንፁሃን ጭፍጨፋ ላይ «ሹተው፣ ነዳጅ ቢኖር አሪፍ ነበር፣ ህንዳዊ መሆን ነው፣ ምሕረት የለንም» የሚሉና ሌሎች የጭካኔ ንግግሮች ሲናገር የነበረውና ከግፍ ፈፃሚዎቹ አንዱ የነበረው የፋሽስቱ ቡድን ቅጥረኛ ወታደር43 ሰዎች በግፍ ረሽነናል ሲል አመነ።
ከዚህ በፊት" እኔ ካሜራ ማን ነኝ፣ የምስሉ ንግግርም የኔ አይደለም "ብሎ የነበረው ሙርከኛው አሁን ግን የአፀያፊው ንግግር ባለቤት መሆኑን ገልፃል።
ያለ ሃጥያቱ የፈሰሰች ደም ሁሌም ፍትህን ትጠላለች። ግፍ እና በደል ፈፃሚዎች ለግዜው ሊደበቁ ቢችሉም እስከ መጨረሻው ግን ኣያመልጡም።
በማህበረ ዴጐ 45 የትግራይ ተወላጅ ወጣቶችን ከአምባገነኑ ኢሳያስ አፈ ወርቂ ወታደሮች ተረክበው፤ በተሰጣቸው ትእዛዝ መሰረት ያለአንዳች ርህራሄ በመጨፍጨፍ የአብይ ቅጥረኛ ወታደሮች አንዱ የነበረው ምርከኛ ስጦታው አለማዬህ በቅፅል ስሙ ፋፊ ነው።
ምርከኛ ወታደር ስጦታው አለማዬህ ከአሁን በፊት እኔ ካሜራ ማን ነኝ ግድያውን ቀርጫሎህ ነገር ግን ገዳዮችን ሌሎች ነበሩ ብሎ ለማወናበድ ሞክሮ የነበረ ሲሆን ከግዜ ብኋላ ግን ህልውናውን ስለሰቀጠጠው ግድያውን ራሱ መምራቱ አምኖ ቃሉ ሰጥቷል።
ከሰውነት ባህሪ በላቀ መልኩ በገዛ አምሳያው የእድሜ እኩያዎቹ ንፁሃን የትግራይ ተወላጆች ላይ የዚህ አይነት ጭካኔ ከየት እንዳመጣው ለሚዲያው ሰው ሁሉ ግራ የሚያጋባ ቢሆንም ምርኮኛው ሰጦታው አለማዬህ ግን ይነገረን የነበረው የጥላቻ ትርክት ነው ያንን ያህል ጨካኝ ያደረገን ይላል።
የንፁሃን የትግራይ ተወላጆች ደም እንደታሰበው በከንቱ ፈሶ የሚቀር አይደለም። የግዜ ጉዳይ ይሆናል እንጂ በመሃል አገርም ይሁን በትግራይ እና በትግራይ ህዝብ ላየረ ግፍ የፈፀሙ፤ ያስፈፀሙ የግፍ ተግባር ያቀደው እና ያስፈፀሙ ሁሉ ከፍትህ ሊያመልጡ እንደማይችሉ የስጦታው አለማዬህ በአብነት የሚጠቀስ ነው።
ጥር 06/2014ዓም
ድምፂ ወያነ ትግራይ
-
- Member
- Posts: 3976
- Joined: 05 Nov 2019, 10:39
-
- Senior Member
- Posts: 12593
- Joined: 27 Jan 2007, 16:30
- Location: Kaliti
- Contact: