ለደሴ ለኮምቦልቻ እና የአካባቢው ነዋሪዎች!! የትግራይ ሰራዊት ከሰላማዊው ሕዝብ ጋር አንዳችም ቁርሾ የለውም:: ይህንን ሕዝባዊ ባህሪውንም አስቀድሞ በተቆጣጠራቸው የተለያዩ የአማራና የዓፋር አካባቢዎች አረጋግጧል::
የትግራይ ሰራዊት እያሳደደ እየቀጣ ያለው፤ በትግራይ ሕዝብ ላይ ግፍና መከራ ዕልቂትና ውድመት ያደረሱትንና፤ አሁንም እንወርሃለን እናወድምሃለን ብለው የሚተኩሱበት ጠላቶቹ ላይ ነው:: ስለዚህ የትግራይ ሰራዊት በሚያደርገው ግስጋሴ በመስጋት፤ በተለይም የደሴና የኮምቦልቻ ነዋሪዎች ቤት ንብረታችሁን ለዘራፊዎች ሳታጋልጡ፤ በአካባቢያችሁ እንድትቆዩ ይመከራል::
ቤት ንብረታችሁን ትታችሁ እንድትሸሹና፤ የዘረፋ ዕቅዳቸውን ለማስፈፀም የተዘጋጁ ወንጀለኞች ናቸው፤ ሆን ብለው፤ "የትግራይ ሰራዊት ይጨፈጭፋችኋል ያርዳችኋል ሽሹ" እያሉ ሕዝቡን በብዛት በማፈናቀል ላይ የሚገኙት:: ለዚህም ማሳያ፤ ይኸው የትግራይ ሰራዊት ወደ ከተማዎቹ ሳይገባ፤ ከወዲሁ በስፋት በሕዝብና የመንግስት ንብረት ዘረፋ ላይ ተሰማርተዋል::
ስለ ደሴና የኮምቦልቻ ሕዝብ ሰላምና ደሕንነት ደንታ የሌላቸው የአብይ ቡድን አባላትም፤ ከሚሸሸው ሰራዊታቸው ጋር አብረው፤ ከነዳጅ ጀምሮ በርካታ ንብረት በማሸሽ ላይ ይገኛሉ:: ቀደም ሲል በተለያዩ አካባቢዎች እንደተረጋገጠው፤ የትግራይ ሰራዊት ሕዝቡንና ንብረቱን ያስጠብቃል እንጂ ኣይነካም:: እንኳንስ ሰላማዊውን የደሴና የኮምቦልቻ ሕዝብ አይደለም፤ ከወንጀል ነፃ የሆኑ የከተማዎቹ አስተዳዳሪዎችም በቦታቸው ላይ ቆይተው፤ የሕዝቡን ሰላምና ደሕንነት ማስከበርና ማሕበራዊ አገልግሎቶን በነበሩበት እንዲያስቀጥሉ ይመከራል:: የትግራይ ሰራዊት፤ በትግራይ ሕዝብ ላይ ግፍና መከራ ያወረዱና የሚተኩሱበትን ጠላቶች ከመቅጣት ውጪ፤ የተቆጣጠራቸውን አካባቢዎች የማስተዳደር ዓላማም ሆነ ግብ የለዉም::
ትግራይ ትስዕር !!
-
- Member
- Posts: 1859
- Joined: 31 May 2013, 21:30
-
- Member+
- Posts: 5299
- Joined: 15 Dec 2013, 03:38
-
- Member
- Posts: 1934
- Joined: 05 Dec 2012, 15:14