Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
MINILIK SALSAWI
Member+
Posts: 9499
Joined: 24 Aug 2012, 12:02

በሕወሓት የጥፋት ኃይል በሰሜን እዝ ጦር ላይ የተፈጸመ እጅግ አስፈሪና ጨካኝነት የተሞላው በጥላቻ የተሞላ ወንጀል ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ የሰጡት ምስክርነት ያዳምጡት

Post by MINILIK SALSAWI » 10 Nov 2020, 10:32

ሌ /ጄኔራል ባጫ ደበሌ በሕወሓት የጥፋት ቡድን በሰሜን እዝ ጦር ላይ ያደረሰውን ግፍ በተመለከተ በዋልታ ቴሌቭዥን ላይ በቀጥታ የሰጡት ምስክርነት ሳዳምጠው ከልብ ያሳዝናል።የሕወሓት ኃይሎች ወታደሮችን ገድለው ልብሳቸውን አውልቀው ሬሳቸውን አንድ ላይ ከምረው ሌሊቱን ሙሉ ሲጨፍሩ አደሩ በዚህ ላይ አሁንም ድረስ አስክሬናቸው አልተቀበረም።አሞራና ጅብ እየበላው ነው። የኦነግን ባንድራ የያዙ የኦነግ ወታደሮች በሽራሮ፣ በራማ፣ በፆረና እና በዛላንበሳ በኩል የሰሜን እዝን ተዋግተዋል። የተፈጸመውን እና እየተፈጸመ ያለውን ግፍ በተመለከተ በዝርዝር አብራርተዋል። ያዳምጡት።




MINILIK SALSAWI
Member+
Posts: 9499
Joined: 24 Aug 2012, 12:02

Re: በሕወሓት የጥፋት ኃይል በሰሜን እዝ ጦር ላይ የተፈጸመ እጅግ አስፈሪና ጨካኝነት የተሞላው በጥላቻ የተሞላ ወንጀል ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ የሰጡት ምስክርነት ያዳምጡት

Post by MINILIK SALSAWI » 10 Nov 2020, 15:20

የአይን ምስክር …. ከአብርሀጅራ እስከ ማይካድራ !!
By Dr Abrham Amare

ወገኖቻችን እጅግ በአሰቃቂ ሁኔታ ተጨፍጭፈዋል ፤ ተረሽነዋል !! ማይካድራ እና አካባቢው ይኖሩ የነበሩ አማራዎች በሙሉ በሚባል ሁኔታ እዛው ነዋሪ በነበሩ ትግሬዎች ታድነዉ ተገድለዋል ። ሁሉም ጎረቤቱን ገድሏል ። ሚስት ባሏን ገድላለች ፤ በሚስቱ በገጀራ ተመቶ ሳይሞት የደረሰን ታካሚም አክመናል። በዚህ ደረጃ የአዉሬነት ተግባር በህዝባችን ተፈፅሟል!!

እኔ በህይወቴ በቀን ዉስጥ ከ200 በላይ ታካሚ ያዉም በድንገተኛ አደጋ ተጎድቶ በአንድ ቀን ዉስጥ ያዉም በአንድ ሆስፒታል ያየሁት ዛሬ ነዉ ። ለወደፊትም ማየቴን እርግጠኛ አይደለሁም ። ስራው እጅግ ቢያደክምም በቁጭት በእልህ የምንችለውን ሁሉ ስናደርግ ዉለናል!!
ለመከረኛዉ የአማራ ህዝብ ይህቺ ማድረግ የምንችላት ትንሽ ነገር ናት!!
~~~~
ህወሃትን እና ጀሌዎችን መረር ብሎ ከመደምሰስ ዉጭ ሌላ ምርጫ የለም ። ምንም ርህራሄ አያስፈልግም !!
በሌላውም የትግራይ አካባቢ የምትኖሩ አማሮች ተደራጅታችሁ ራሳችሁን ጠብቁ ፤ ራሳችሁን ከሞት ታደጉ!!

MINILIK SALSAWI
Member+
Posts: 9499
Joined: 24 Aug 2012, 12:02

Re: በሕወሓት የጥፋት ኃይል በሰሜን እዝ ጦር ላይ የተፈጸመ እጅግ አስፈሪና ጨካኝነት የተሞላው በጥላቻ የተሞላ ወንጀል ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ የሰጡት ምስክርነት ያዳምጡት

Post by MINILIK SALSAWI » 11 Nov 2020, 01:52

Please wait, video is loading...

MINILIK SALSAWI
Member+
Posts: 9499
Joined: 24 Aug 2012, 12:02

Re: በሕወሓት የጥፋት ኃይል በሰሜን እዝ ጦር ላይ የተፈጸመ እጅግ አስፈሪና ጨካኝነት የተሞላው በጥላቻ የተሞላ ወንጀል ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ የሰጡት ምስክርነት ያዳምጡት

Post by MINILIK SALSAWI » 11 Nov 2020, 07:23

በኦሮሚያ በአዲስ አበባ እና በአማራ ክልሎች በመከላከያ ሰራዊት ላይ የፈጸመውን ጥቃት የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ መታቀዱን የክልሎቹና የከተማ አስተዳደሩ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

ህገ ወጡ የህወሓት ቡድን እየፈጸመው ያለውን ግፍ ለመላው ዓለም ለማሳወቅ ሰላማዊ ሰልፍ ነገ ይደረጋል

https://mereja.com/amharic/v2/393033

MINILIK SALSAWI
Member+
Posts: 9499
Joined: 24 Aug 2012, 12:02

Re: በሕወሓት የጥፋት ኃይል በሰሜን እዝ ጦር ላይ የተፈጸመ እጅግ አስፈሪና ጨካኝነት የተሞላው በጥላቻ የተሞላ ወንጀል ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ የሰጡት ምስክርነት ያዳምጡት

Post by MINILIK SALSAWI » 11 Nov 2020, 08:45

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ከትግራይ ልዩ ሃይል ጋር በማበር በአገር መከላከያ ሰራዊት ጥቃት የተሳተፉ አባላቱን እያጠራ መሆኑን አስታወቀ።

ኢትዮ ኤፍ ኤም - የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ኦነግ ከታጠቁ እና ጸረ -ሰላም ከሆኑ ሀይሎች ጋር ግንኙነት ያላቸውን አባላቱን በመለየት እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል፡፡

የግንባሩ ቃላ ቀባይ አቶ ቀጀላ መርዳሳ ለኤትዮ ኤፍ ኤም እንዳሳወቁት ከሰሞኑ በተለያዩ የመንግስት መግለጫዎች ከህወሃት ቡድን ጋር የኦነግ ሸኔ አባላት በጦርነቱ መሳተፋቸው ተነግሯል፡፡

ይሆን እንጂ ኦነግ የሚለው ስም ከዚህ ተቀጥሎ እንዳይጠራ እየተነጋገርን ነው ብለዋል፡፡

ምክንያቱም እኛ ከሸኔ ጋር ግንኙነት የለንም ፤የታጠቀ ሰራዊትም የለንም ነው ያሉት፡፡

ኦነግ በሰላማዊ መንገድ የፖለቲካ ምህዳሩን ተቀላቅሏል፣ የምንሰብቀው ጦርም የለም በእኛ ስም የሚንቀሳቀስ የታጠቀ ሃይል ካለ መንግስት እርምጃ ይውሰድ ሲሉ ተናግረዋል፡፡

እንዲህ አይነት ተግራት ላይ የሚሳተፉ እንዲሁም በተዘዋዋሪ ደግሞ ድጋፍ የሚሰጡና የሚያሰባስቡ አባላቶቻችንን እየለየን ነው ብለዋል አቶ ቀጀላ፡፡

መንግስት በሚሰጣቸው መግለጫዎች የኦነግ ሸኔ አባላት ሳይሆን የሸኔ ታጣዊዎች እንዲልም አሳስበዋል፡፡

አቶ ቀጀላ እንዳሉት በቀደመው ዘመን ሸኔ ማለት የስራ አስፈጻሚ አባላት የሚጠሩበት እንደነበር አስታውሰው በኃላ ላይ ግን ይህንን ስም አሁን የስራ አስፈጻሚ ኮሚቲ በሚል እየተጠራ ነው ብለውናል፡፡ ኢትዮ ኤፍ ኤም
-

MINILIK SALSAWI
Member+
Posts: 9499
Joined: 24 Aug 2012, 12:02

Re: በሕወሓት የጥፋት ኃይል በሰሜን እዝ ጦር ላይ የተፈጸመ እጅግ አስፈሪና ጨካኝነት የተሞላው በጥላቻ የተሞላ ወንጀል ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ የሰጡት ምስክርነት ያዳምጡት

Post by MINILIK SALSAWI » 12 Nov 2020, 07:47

ዶ/ር ደብረፅዮንን ጨምሮ በወንጀል የተጠረጠሩ የምክር ቤት አባላት ያለመከሰስ መብት ተነሳ

Read More - https://mereja.com/amharic/v2/394098

ስግብግቡ የሕወሓት ቡድን በመከላከያ ሠራዊት ላይ ያደረሰውን ጥቃት የሚያወግዙ ሰላማዊ ሰልፎች በክልል ከተሞች ተካሔዱ

Read More - https://mereja.com/amharic/v2/393959


MINILIK SALSAWI
Member+
Posts: 9499
Joined: 24 Aug 2012, 12:02

Re: በሕወሓት የጥፋት ኃይል በሰሜን እዝ ጦር ላይ የተፈጸመ እጅግ አስፈሪና ጨካኝነት የተሞላው በጥላቻ የተሞላ ወንጀል ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ የሰጡት ምስክርነት ያዳምጡት

Post by MINILIK SALSAWI » 12 Nov 2020, 13:35

የ4ኛ ሜካናይዝድ አዛዥ ሰራዊቱን በማታለልና ደባ በመስራት ጥቃት እንዲፈጸምበት የመሪነቱን ሚና ተጫውተዋል - የሰሜን እዝ አባላት

(ኤፍ.ቢ.ሲ) “የ4ኛ ሜካናይዝድ አዛዥ ኮሎኔል ገብረስላሴ በላይ ሰራዊቱን በማታለልና ደባ በመስራት ጥቃት እንዲፈጸምበት የመሪነቱን ሚና ተጫውተዋል” ሲሉ ጥቃቱን ተከላክለው የተረፉ የሰሜን እዝ አባላት ተናገሩ።
“በፅንፈኛው የህወሃት ታጣቂ ሃይል የተፈፀመብን ጥቃት ከፍተኛ ክህደት ነው” ገልጸዋል።
-
ፅንፈኛው የህወሃት ቡድን ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ምሽት ላይ በሰሜን እዝ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ላይ አሳፋሪ ጥቃት ማድረሱ ይታወቃል።
የጁንታው ታጣቂ ሃይል በፈፀመው አስነዋሪ ድርጊት የእዙ አባላት ላይ ጉዳት የደረሰ ቢሆንም የአገር መከላከያ ሰራዊት ጥቃቱን መክቶ በፅንፈኛው ሃይል ላይ ህግ የማስከበር ተግባር እየፈፀመ ይገኛል።
-
ከፅንፈኛው ቡድን ጥቃት ተከላክለው የተረፉ የሰሜን እዝ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እንዳሉት፥ የተፈጸመው ጥቃት በታሪክ ከፍተኛ ክህደት ነው።
ከሰሜን አዝ አባላት መካከል ፅንፈኛውን ሃይል በመከላከል የተረፉት አስር አለቃ ዋለልኝ ወርቅነህ እንደሚሉት፥ የአገር አለኝታ በሆነ ሰራዊት ላይ እንዲህ አይነት አስነዋሪ ተግባር የትም አገር ተፈፅሞ አያውቅም።
-
“በተለይ የ4ኛ ሜካናይዝድ አዛዥ የሆኑት ኮሎኔል ገብረስላሴ በላይ ሰራዊቱን በማታለልና ደባ በመስራት የመሪነቱን ሚና ተጫውተዋል” ብለዋል።
የጁንታው ቡድን ህይወቱን ለአገር አሳልፎ በሚሰጠው ጀግናው የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ ጥቃት በማድረስ ወደ ዝርፊያ መግባታቸውንም ተናግረዋል።
ጥቃቱ በተፈፀመበት እለት የሰሜን እዝ 4ኛ ብርጌድ አዛዥ ኮሎኔል ገብረስላሴ በላይ የመከላከያ ሰራዊቱን መኪና ታርጋ በመቀየርና ሌሎች ተንኮሎችንም በመፈፀም አስጠቅተውናል ሲሉም ተናግረዋል።
-
በሰሜን እዝ 4ኛ ሜካናይዝድ 2ኛ ብርጌድ የብሬን ምድብተኛ ወታደር አዱኛ እምሩ የጁንታው ቡድን ምሽት ላይ ከበባ በማድረግ ያልታሰበ ጥቃት እንደሰነዘረባቸው አስታውሶ፤ ህወሃት ያስታጠቃቸው የልዩ ሃይልና ሚሊሻ አባላት ከጁንታው ጋር ተባብረው ጥቃቱን እንደፈፀሙባቸውም ተናግሯል።
ከእዙ መካከል አስር አለቃ ወርቅነሽ ሰለሞንም የሰሜን እዝ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ በህወሃት ቡድን የተፈፀመው ክህደት የባንዳነት ተግባር መሆኑን ተናግራለች።
-
ሰራዊቱ ለትግራይ ህዝብ አንበጣን በመከላከል፣ ጤፍ በማጨድ፣ ጤና ጣቢያና ትምህርት ቤት በመገንባት አገልጋይ እንደነበርም አስታውሳለች።
የሰራዊቱ አባላት ካላቸው ገንዘብ በማዋጣት ወላጆቻቸውን ያጡ ህጻናትን ያስተምሩ እንደነበርም ገልጻለች።
“ነገር ግን በከሃዲው ቡድን በታሪክ ተደርጎ የማያውቅ ክህደት ተፈፅሞብን ባጎረሰ እጃችን ተነክሰናል” ብላለች።
“ጁንታው የህወሃት ቡድን የፈጸመው አገርን የማፈራረስ አላማ የባነዳነት ድርጊት መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሊያወግዘው ይገባል” ነው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

MINILIK SALSAWI
Member+
Posts: 9499
Joined: 24 Aug 2012, 12:02

Re: በሕወሓት የጥፋት ኃይል በሰሜን እዝ ጦር ላይ የተፈጸመ እጅግ አስፈሪና ጨካኝነት የተሞላው በጥላቻ የተሞላ ወንጀል ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ የሰጡት ምስክርነት ያዳምጡት

Post by MINILIK SALSAWI » 12 Nov 2020, 14:23

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግላጫ እንደገለጸው፤ የጁንታው የሕወሓት ወንበዴ ቡድንን በበላይነት በመምራት በትግራይ ክልል በሚገኘው በሀገር መከላከያ ሰራዊት ሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት በመፈፀም የአገር ክህደት ወንጀል የፈጸሙት የጁንታው የጥፋት ቡድን አባላትን አድኖ ለህግ ለማቅረብ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ወጥቷባቸዋል፡፡
የጥፋት ቡድኑ አባላት ከኦነግ ሸኔ እና ከሌሎች ፀረ-ሰላም ሃይሎች ጋር በመቀናጀትም ከተለያዩ ክልሎች አገርን የማፍረስ ተልዕኮ ያለቸውን ኃይሎች በመመልመል ትግራይ ክልል ድረስ በመውሰድ ለእኩይ ተልዕኮቸው ስኬት የተለያዩ ስልጠናዎችን በመስጠት እንዲሁም የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፎችን በማድረግ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ብሄርን ከብሄር በማጋጨት እና በሃይማኖት ሽፋን ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር በማድረግ በርካታ ንፅሁን ዜጎች እንዲገደሉ፣ በአካልና በንብረት ላይም ከባድ ጉዳት እንዲደርስ ማድረጋቸውን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በላከው መግለጫ አመልክቷል፡፡
እነዚህ የሀገር ህልውናን አደጋ ላይ በመጣል እንዲሁም ህገ-መንግስቱንና ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በሀይል በመናድ ወንጀል የሚፈለጉትና የፍርድ ቤት የመያዣ ትዕዛዝ የወጣባቸው፡-
1.ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል
2.ጌታቸው ረዳ
3. ፈትለወርቅ ገ/እግዝያብሄር
4. አስመላሽ ወ/ስላሴ
5.ዶ/ር አብርሃም ተከስተ
6.ኪሪያ ኢብራሂም
7.ረዳይ አለፎም
8.አማኑኤል አሰፋ
9.ዶ/ር አትንኩት መዝገቡ
10.ኪሮስ ሀጎስ
11.ያለም ፀጋ
12.ሰብለ ካህሳያ
13.ጌታቸው አሰፋ
14.ዳንኤል አሰፋ
15.ኢሳያስ ታደሰ
16.ዶ/ር አክሊሉ ሀ/ሚካኤል
17.አለም ገ/ዋህድ
18.ተክላይ ገ/መድህን
19.ዶ/ር እያሱ በርሄ
20.ዶ/ር ረዳይ በርሄ
21.ዶ/ር ኪዳን ማርያም በርሄ
22.ነጋ አሰፋ
23.ሺሻይ መረሳ
24. ዶ/ር ገ/ህይወት ገ/እግዝያብሄር
25. አፅብሃ አረጋዊ
26.ዶ/ር ኢ/ር ሰለሞን ኪዳኔ
27.ሀዱሽ ዘነበ
28.በርሄ ገ/እየሱስ
29.ይትባረክ አምሃ
30.ዶ/ር ገ/መስቀል ካህሳይ
31.ዶ/ር ፍስሃ ሀ/ፂዮን
32.ርስቀ አለማየው
33.ዶ/ር አዲስ አለም ቤሌማ
34.ዘነበች ፍስሃ
35.ፍሬወይኒ ገ/እግዝያብሄር
36.አቶ ስዩም መስፍን
37.አቶ አባይ ፀሐዬ
38.እያሱ ተስፋይ
39.ለምለም ሀድጎ
40.ፕሮፌሰር ክንድያ ገ/ህይወት
41.ሀብቱ ኪሮስ
42.በየነ ምክሩ
43.ካሳዬ ገ/ህይወት
44.ሩፈኤል ሽፈራ
45.ሊያ ካሳ
46.ተወለደ ገ/ፃዲቅ
47.ሙሉ ገ/እግዝያብሄር
48.ኪሮ ስጉዑሽ
49.ዶ/ር አማኑኤል ሀይሌ
50.ደሳለኝ ተፈራ
51.ኢንጅነር አርአያ ብርሀኔ
52.አልማዝ ገ/ፃድቅ
53.ሰለሞን መአሾ
54.ተኪኡ ማዕሾ
55.ገነት አረፈ
56.ብርክቲ ገ/መድህን
57.ዶ/ር ሀጎስ ገዳፋይ
58.ዘራይ አስጎዶም
59.አሰፋ በላይ
60.አቶ ሸዋንግዘው ገዛኸኝ
61.አፅብሃ ግደይ
62.አቶ ስብሀት ነጋ
63.አቶ ሴኮትሬ ጌታቸው
64.በሪሁን ተ/ብርሃን የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ዳኛ የነበረ ናቸው፡፡
ከላይ ስማቸው የተዘረዘረው የወንበዴው የጁንታው ሕወሓት የጥፋት ቡድን አባላት የአገር ክህደት ወንጀል ከመፈጸማቸውም በተጨማሪ በከፍተኛ የአገር ሃብት ምዝበራና ዘረፋ እንዲሁም በሰበአዊ መብት ጥሰት ወንጀልም ጭምር የሚፈለጉ መሆናቸውን ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በመግለጫው አሳውቋል፡፡
በተመሳሳይም ከጁንታው ሕወሓት ቡድን አባላት ጋር እየተገናኙ የሀገር ክህደት ወንጀል በፈፀሙና አገር በማፍረስ ሴራ በተሳተፉ የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና የፖሊስ አመራሮች ላይም የፍርድ ቤት የመያዣ ትዕዛዝ እንደወጣባቸው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በመግለጫው አስታውቋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ መንግስት እና ሕዝብ የጣለባቸውን አገራዊ ኃላፊነትና ህገመንግስታዊ ግዴት ወደጎን በመተው መቀመጫዉን ትግራይ ክልል ካደረገዉ ከወንበዴው የህወሃት የጁንታው ቡድን አባላት ተልዕኮ በመቀበል በሰሜን ዕዝ ሰራዊት አባላት ውስጥ ሴሎችን በማደራጀት ከማዕከል የነበረው ግንኙነት እንዲቋረጥና ጥቅምት24 ቀን 2013 ዓ/ም ጥቃት እንዲፈጸም በማድረግ የሞት፣የአካል ጉዳት እና የጦር መሳሪያ ዝርፊያ እንዲፈፀም ማድረጋቸውን የኮሚሽኑ መግለጫ ያመለክታል፡፡
ባለፉት 21 አመታት በምሽግ አብረው ሲኖሩ የነበሩ ጓዶቻቸውን የጁንታው ቡድን እኩይ አላማ ማስፈጸሚያ በማድረግ አገር በማፍረስ ተልዕኮው በመምራትና በመሳተፍ የሚፈለጉት ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖችና የፖሊስ አባላት፡-
1.ሌ/ጀኔራል ታደሰ ወረደ ተስፋዬ (ውድወርደ)
2.ሜ/ጄኔራል ዮሐንስ ወ/ጎርጊስ ተስፋይ (መዲድ)፣
3.ሜ/ጄኔራል ብርሃነ ነጋሽ በየነ (ውድመድህን)፣
4.ብ/ጄኔራል ሀ/ስላሴ ግርማይ ገ/ሚካኤል
5.ብ/ጄኔራል ምግበ ሃይለ ወ/አረጋይ (አባበርሃ፣)
6.ሜ/ጄኔራል ኢብራሂም አብዱልጀሊል መሀመድዙን
7.ብ/ጄኔራል ገ/ኪዳን ገ/ማርያም የእብዮ
8.ሜ/ጄኔራል ገብረ ገ/አድሃና ወ/ዘጉ (ገብረዲላ)
9.ሜ/ጄኔራል ገ/መስቀል ገ/ዮሀንስ /አስቴር/
10.ብ/ጄኔራል አብርሃ ተስፋይ በርሄ /ድንኩል/
11.ብ/ጄኔራል ፍስሃ በየነ (ወርቅአይኑ)
12.ሜ/ጄኔራል ህንፃ ወ/ጎርጊስ ዮሐንስ
13.ብ/ጄኔራል አለፎም አለሙ ወ/ማርያም /ቸንቶ/
14.ብ/ጄኔራል ገ/መስቀል ገ/እግዝያብሄር (ጠቀም)
15.ብ/ጄኔራል ተ/ብርሃን ወ/አረጋዊ
16.ሜ/ጄኔራል አታክልቲ በርሄ ገ/ማርያም
17.ኮሚሽነር መኮንን ካህሳይ ገ/መስቀል (ፅንቡላ) የትግራይ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር
18.ም/ኮሚሽነር መንግስቴ አረጋዊ የትግራይ ክልል ፖሊስ ም.ኮሚሽነር
19.ኮ/ር ጌታቸው ኪሮስ የትግራይ ፖሊስ አመራር የነበረ
20.ም/ኮሚሽነር ግርማይ ከበደ (ማንጁስ/ የፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ዘርፍ ሃላፊ የነበረ 21.ም/ኮሚሽነር ተክላይ ፀሃዬ የፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ዘርፍ ም/ሃላፊ የነበረ
22.ኮ/ር ንጉስ ወ/ገብርኤል የትግራይ ልዩ ሃይል ፖሊስ ሃላፊ፣
23.ኮ/ር ገ/ስላሴ ታፈረ የፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል አመራር የነበረ
24.ኮ/ር ፍስሃ ተ/ማርያም (ወዲአርባ) የፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል አመራር የነበረ
25.ኮ/ር ተስፋዬ ገ/ኪዳን (ተስፋዬ ባንዳ) የፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል አመራር የነበረ 26.ሜ/ጀነራል ገ/መድህን ፍቃዱ ሃይሉ (ውድነጮ) በቁጥጥር ስር የዋሉ
27.ሜ/ጀነራል ይርዳው ገ/መድህን ገ/ፃድቅ(አስቴር)በቁጥጥር ስር የዋሉ
28.ብ/ጀነራል ገ/ህይወት ሲስኖስ ገብሩ በቁጥጥር ስር የዋሉ
29.ብ/ጀነራል ኢንሶ እጃጆ እራሾ በቁጥጥር ስር የዋሉ
30.ብ/ጀነራል ፍስሃ ገ/ስላሴ እንሁን በቁጥጥር ስር የዋሉ
31.ኮ/ል ደሳለኝ አበበ ተስፋዬ በቁጥጥር ስር የዋሉ
32.ኮ/ል እያሱ ነጋሽ ተሰማ በቁጥጥር ስር የዋሉ
መላው የሃገራችን ህዝቦች፤የሀገር መከላከያ ሰራዊት፤የአገራችን የፖሊስ ሰራዊትና የደህንነት ተቋማት እነዚህን የጁንታውን የሕወሓት የጥፋት ቡድን ተፈላጊዎች አድኖ ለህግ ለማቅረብ እየተደረገ ባለው ጥረት በያላችሁበት የድርሻችሁን እንድትወጡ ኮሚሽኑ ጥሪ እያቀረብ፤ በተለይም ደግሞ የትግራይ ህዝብ፤የክልሉ ልዩ ሀይል አባላትና ሚሊሻዎች፤ የጁንታው የሕወሓት ወንበዴ ቡድን ልጆቻቸውንና ቤሰተቦቻቸውን በወጭ አገራት በድሎትና በቅንጦት እያኖሩ የድሃውን የትግራይ ህዝብ ልጅ ለእኩይ አላማቸው መፈጸሚያ ከእሳት እየማገዱ በመሆኑ ይህንን ተገንዘበን ይሄንን የጥፋት ቡድን አድናችሁ በመያዝ ለመንግስት የፀጥታ ሀይል እንድታስረክቡ ጥሪ ያቀርባል፡፡
በመጨረሻም የጁንታው ሕወሓት ወንበዴ ቡድን ተፈላጊዎችን በዝርዝር እየገለፅን የምንሄድ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን እናሳውቃለን፡፡

MINILIK SALSAWI
Member+
Posts: 9499
Joined: 24 Aug 2012, 12:02

Re: በሕወሓት የጥፋት ኃይል በሰሜን እዝ ጦር ላይ የተፈጸመ እጅግ አስፈሪና ጨካኝነት የተሞላው በጥላቻ የተሞላ ወንጀል ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ የሰጡት ምስክርነት ያዳምጡት

Post by MINILIK SALSAWI » 13 Nov 2020, 08:09

የህዝብን የትኩረት አቅጣጫ ለማስቀየር የተከዜ ግድብ በቦንብ እንደተመታ የሚያትት ሆን ተብሎ የተቀናበረ፣ የሀሰት መረጃን ህወሓት አሰራጭቷል።

https://mereja.com/amharic/v2/395178



MINILIK SALSAWI
Member+
Posts: 9499
Joined: 24 Aug 2012, 12:02

Re: በሕወሓት የጥፋት ኃይል በሰሜን እዝ ጦር ላይ የተፈጸመ እጅግ አስፈሪና ጨካኝነት የተሞላው በጥላቻ የተሞላ ወንጀል ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ የሰጡት ምስክርነት ያዳምጡት

Post by MINILIK SALSAWI » 14 Nov 2020, 11:03

የሰሜን ዕዝ ላይ ቀድመን እርምጃ በመውሰድ በ45 ደቂቃ ውስጥ ዕዙን በሙሉ መቆጣጠር ችለናል። ሴኩተሬ ጌታቸው

ሰሜን እዝን ቀድመው ማጥቃታቸውን እርምጃም መውሰዳቸውን የሕወሓት አመራሮች አምነዋል።

https://mereja.com/video2/watch.php?vid=d83778121



MINILIK SALSAWI
Member+
Posts: 9499
Joined: 24 Aug 2012, 12:02

Re: በሕወሓት የጥፋት ኃይል በሰሜን እዝ ጦር ላይ የተፈጸመ እጅግ አስፈሪና ጨካኝነት የተሞላው በጥላቻ የተሞላ ወንጀል ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ የሰጡት ምስክርነት ያዳምጡት

Post by MINILIK SALSAWI » 14 Nov 2020, 11:48

ራያ ዋጃና ጥሙጋ ቆቦ ወ አዘቦ ጨርጨር መሆኒ እና ባላ ከእልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ በሁዋላ የባርነት ቀንበራቸው ተሰብሯል:: የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አላማጣንና ኮረምን ከህወሀት ሰራዊት ነፃ አድርጎ ግስጋሴውን ቀጥሏል::

https://mereja.com/amharic/v2/396470






MINILIK SALSAWI
Member+
Posts: 9499
Joined: 24 Aug 2012, 12:02

Re: በሕወሓት የጥፋት ኃይል በሰሜን እዝ ጦር ላይ የተፈጸመ እጅግ አስፈሪና ጨካኝነት የተሞላው በጥላቻ የተሞላ ወንጀል ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ የሰጡት ምስክርነት ያዳምጡት

Post by MINILIK SALSAWI » 15 Nov 2020, 11:13

ጽንፈኛው የሕወሓት ቡድን የተከዜ ግድብ ተደብድቧል ሲል ያሰራጨው መረጃ ሀሰት ነው–የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
*****************
ጽንፈኛው የህወሓት ቡድን “የተከዜ ኃይል ማመንጫ ግድብ በጦር ጄት ተደብድቧል” ሲል ያሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑን የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል አስታወቀ።የጽንፈኛው የህወሓት ቡድን መሪ ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በቅርቡ በሰጡት መግለጫ “የኢትዮጵያ አየር ኃይል የተከዜ ኃይል ማመንጫ ግድብን ደብድቧል” ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል።የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሞገስ መኮንን ዛሬ ለኢዜአ እንደተናገሩት፣ ጽንፈኛው ቡድን ግድቡን በሚመለከት የተሳሳተ መረጃ እያሰራጨ ይገኛል።

የቡድኑ ታጣቂዎች ከቀናቶች በፊት ግድቡን በኃይል ለመቆጣጠር በማለም በጥበቃ ሥራ በተሰማሩ የፌዴራል ፖሊስ አባላቶች ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን አስታውሰዋል።“ጥቃቱን ለመፈጸም በከፈቱት ተኩስ በግድቡ የኃይል ማስተላለፊያ ስዊች ላይ ጉዳት አድርሰዋል” ነው ያሉት።በአሁኑ ወቅትም የቡድኑ አፈ-ቃላጤዎች የኃይል ማመንጫ ግድቡ በኢትዮጵያ የጦር ጄት እንደተደበደበ አድርገው የሀሰት መረጃ እያሰራጩ እንደሚገኙ ተናግረዋል።የጽንፈኛ ቡድኑ ታጣቂዎች የኃይል ማስተላለፊያ ‘ስዊች’ ላይ ካደረሱት ጥቃት ውጪ በግድቡ ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለመድረሱን አብራርተዋል።ግድቡ የያዘው 9 ነጥብ 3 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሊትር ውሃ መደበኛ ፍሰቱን ጠብቆ ወደታችኛው ተፋሰስ እየወረደ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ “ይህም ቡድኑ ስለግድቡ ያሰራጨው መረጃ ሀሰት ስለመሆኑ ማሳያ ነው” ብለዋል።







Post Reply