ሲንምቤ 11 ሚባልውን ጉራጌ ጠል ዎያኔን እርሳውና የምሬ እውነትኛ ነገር ልንገርህ ። በነገራችን ላይ ኖብል በጉራጌኛ ወለባ ይባላል ። ይህ ያንተ ስህተት ሳይሆን የኦርቶዶክስ ታሪክ ታሪክ ነጋሪዎች ስለ ዝዋይ፣ አዳዲ (ታላቅ አያት አጋ ይባላል፣ ታላቅ ሴት አያት አዳዳ ትባላልች፣ አዶት እናት ማለት ነው) የታላቋ እናት ማሪያም ቤተ መቅድስ ማለት ነው)።
አዳዲ ማሪያም፣ ዝቋላ አቦ፣ ምድረ ከብድ አቦ እና ሌሎች ብዙ ብዙ የጉራጌ ገዳማት እነቆንዳልቲቲ በአለ ወልድን ያቆሙት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (ጉራጌ ቅዱስ አቦ ይላቸዋል) ናቸው ። ያ የሆነው በ1460ቹ ማለትም ከግራኝ ወረራ 50 አመት በፊት ነበር። ቅዱስ አቦ አርፈው የተቀበሩት በሰሜን ጉራጌ በምድረ ክብድ አቦ ገዳም ነው ። ያ ዝክረ እረፍታቸው ነው በግንቦት አምስት በምድረ ክብድ የሚከበረው ። (ከታች ቪዲዮ አሳይሃልሁ)።
አዉ የምድረ ክብድ አቦ፣ የዝቋል አቦ፣ ያዳዲ ማሪያም፣ የዝዋይ (የዛይ ላቄ) ገዳማት ሁሉ ያቆሙትና በግራኝ ነደው ከዚያ በጋላ ከመወረራችው በፊት የጉራጌ አገር ነበሩ ።
ግን ይህን ልብ በል ። በላስታ የገነነው የዛጉዌ ስርው መንግስት ያበቃው በ1270 ነው ። ማለትም አዳዲና ዝቋላ ከመቆማችው 200 አመት በፊት ። እኔ ወጣት የኦርቶዶክስ ተራኪዎች ይህን ሲናግሩ አፍራለሁ፣ ለምን ቢባል ትንሽ ታሪክ ቢያገላብጡ የግዜው ልዩነት በጣም ግዙፍ ስለሆነ።
ላሊበላ ለምን መጣ በል? ክግራኝ እና የጋላ ወረራ በኋላ ለክርስቲያኖች ክባድ ዘምን ነበር። የገዳ ወረራ በየ8 አምቱ የስው ቤትም ሆን ቤተ ክርስቲያን በወራሪ ይቃጠሉ ስለ ነበር የዋሻ ቤተ መቅድስ ባህል ግዴታ ሆነ ። አዳዲም ዋሻ የገባችው ከ1525 በኋላ ነው ። የየካው ዋሻ ሚካኤል ብቻ ሳይሆን ብዙ የዋሻ ገዳማት በጉራጌ አሉ። ያ ነው ሃቁ
ጉራጌ በጣም ጥንታዊ የሴም ሕዝብ ነው ። ለዚያ ማሳያው ቋንቋው ነው ። ያ ጥንታዊ ቁንቋ ለግዕዝ በጣም የቀረበ ነበር፣ ዛሬም ብዙ ብዙ ቃላቶቻችን ግ ዕ ዝ ናችው። አው ብዙ ጉራጌ ጎሳዎቹ ወደ ኦሮሞ ተለውጠዋል፣ ለምሳሌ ገላን፣ ያያ (በቾ)፣ ሜታ፣ አጃጄ ሌሎችም ዛሬ ኦሮሞች ናችው ። በደቡብና ምዕራብ (ሰባት ቤት ጥቂት ያዲያ ድብልቅ ና በእንደ ጋኝ የወላይታ ድብልቅ አሉ ። በሰሜን ጂዳ የሚባሉ የኦሮሞ ድብልቅ አሉ። ልክ እንድ ቀረው ኢትዮጵያ ሕዝብ ማለት ነው።