አሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ የፖለቲካ እውቀትና ብስለት የት እንደ ደረሰ የሚታይበት ወቅት ላይ ደርሰናል ። ምን ማለቴ ነው?
የመንግስትን ቀን ተቀን ስራ በአይነ ቁራኛ የሚጠብቁት ረድፎች አንደኛ ሚዲያ፣ ሁልተኛ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ሶስተኛ የሲቪል ማህበሮችና አራተኛው ሕዝቡ ለምሳሌ ግለሰብ ምሁራን ወዘተ ናቸው ። እስካሁን ከሚዲያ ሌላ የቀሩት ቁራዎች ብዙም አይሰሙም ።
እንደ ሚታወቀው የመንግስት ፖሊሲ የሚቀርጹና መንግስትን የሚመሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ናቸው ። የፖለቲካ ፓርቲዎች ያገርና የመንግስት ጥቅም ብቻ ሳይሆን የያንዳንዱ መደብ፣ የሕዝብ አካል፣ ቡድን ፣ ረድፍ ትቅም በፖሊሲያቸው በማካተት መንግስት የመምራትና በመንግስት ላይ ተጽኖ ፈጣሪዎች ናቸው።
ነገር ግን የፖለቲካ ፓርቲዎችን ስራ በአይነ ቁራኛ የሚጠብቅ፣ የሚደግፍ፣ የሚተች ማነው? ያ ከላይ ያሉት የሚዲያው፣ የሲቪል ማህበራትና ሰፊው ሕዝብ (ምሁር፣ ነጋዴ፣ ደበሬ፣ ወዘተ) ናቸው ስለሆነም ...
ለምሳሌ ለሚቀጥለው የፓርቲዎች ውይይት 4 ትላልቅ ያጀንዳ ርዕሶች ተመድበዋል ፤ እንሱም ...
ሕገ መንግስትና ሕገ ማንግስታዊነት
ታላቁ የኢትዮጵያ አገራዊ ተቃርኖ ምንድን ነው?
የፖለቲካ ፓርቲዎች አደረጃጀት
ከፓርቲዎች አረጃጀት አኳያ ትክክለኛ ምርጫ እንዴት ማካሄድ ይቻላል?
ናቸው ። ይህ ሆኖ ሳለ ...
እስካሁን ድረስ የሚዲያው ሆነ፣ የሲቪሉ ረድፍ፣ ወይም የሕዝቡ አካላት እነዚህን 4 አጀንዳዎች በሚመለከት ፓርቲዎች የሚያቀርቡት ሃሳብ የለም ። ፓርቲዎች ላይ ገምቢም ሆነ ሂሳዊ ተጽኖ ሲያደርጉ አይታይም ።
ይህ ሁሉ የሚያሳየው ህብረተሰባችን ሌት ተቀን ፖለቲካ መሰል ነገሮች ቢነታረክም አንድ የፖለቲካ ኮሚኒቲ ፣ ማቹር የፖለቲካ ኮሚኒቲ ማድረግ የሚገባውን ማድረግ እንዳልጀመረ ነው ።