Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Horus
Senior Member+
Posts: 30668
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

አቢይ አህመድ፤ የኢትዮጵያ ከማል አታቱርክ? በታማኝ ኢትዮጵያዊና በጎሳ ባንዳ መሃል ያለው ግዙፍ ትግል !!!

Post by Horus » 31 Jul 2020, 01:12

ይህ ረዕስ ገና ብዙ የሚባልበት፣ ብዙ የሚዘረዘር ጉዳይ ነው ። ለዛሬና ለመጀመር ይህን ልበል።

እኔ ከኤርሚያ ለገሰ ጋር እስማማለሁ፤ አቢይ የኦሮሞ ብሄረተኛ አይደለም ። የስልጣን ብሄረትኛ የሚለው አባባል ሳይንሳዊ ብቻ ሳይሆን መሆን ያለበትና የሚሆነውም ነው ። ማንኛውም የፖለቲካ እንሰሳ ስለመንግስት ሲያስብ ያለው ነገር የፖለቲካ ስልጣን ነው ። አቢይ የፖለቲካ ስልጣን መያዝና ያንን ስልጣን ሌላው እንዳይቀማው መከላከሉ የፖለቲካኛነቱ መገለጫ ነው ።

ጥያቄው ይህ ሰው የፖለቲካ ስልጣኑን በኢትዮጵያ አጀንዳ ላይ ነው የሚጠቀምበት? ወይስ ላንድ ጎሳ ጥቅምና የውስጥ ባንዳ በመሆን? ይህ ነው ልዩነቱ !! እኔ አቢይ የኢትዮጵያን አጀንዳ እስካራማደ ድረስ እንዲያውም የኢትዮጵያ ከማል አታቱርክ ይሁን ባይ ነኝ ።

አቢይ አህመድ ከኢትዮጵያ ታላላቅ መሪዎች አንዱ ለመሆን ጥቂት የቀሩ ነገሮችን ማድረግ አለበት፤ ክልሎችን ማፍረስ፣ አዲስ ሕገ መንግስት ማምጣት፣ የጎሳ ፌዴሬሽንን ማፍረስ እና የጎሳ ፓርቲዎችን ሕገ ወጥ አስደርጎ ወደ ሲቪክ ማህበርነት መመደብ ። ይህን ካረገ አቢይ ከነምኒልክ፣ ከነ ሃይለ ስላሴ ተርታ እንደሚመደብ ጥርጥር የልውም! ለዚህ ሁሉ የመላ ኢትዮጵያ ድጋፍ አለው ፤ እሱ የፖለቲካ ቆራጥነት ካለው !!

ለምሳሌ የሰሞኑ ከፓርቲዎች ያደረገውን ወይይት ልብ በሉ ! አስገራሚ ያቋም መግለጫ መድረክ ነበር። ማለትም አቢይ አህመንድ የፖለቲካ መሰረቱን፣ የድጋፍ መቆሚያውን፣ የመንግስቱ ሶሺያል መሰረት ከጎሳ ሃይሎች ወደ ኢትዮጵያዊ ሃይሎች ማሸጋገሩን ፣ መለወጡን ያወጀበት እጅግ ወሳኝ መድረክ ነበር ። ይህም ማለት አሁን ..

ብዙ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ከአቢይ ፓርቲ ጋር እንዴት ማበርና መቀናጀት እንዳለባቸው የምር ማሰብ አለባቸው። ቢያንስ የጎሳ ባንዳ መደቦች ሙሉ በሙሉ እስከ ሚሸነፉ ያቢይ ደጋፊ የሆነው ብልጽግና ፓርቲ እና እንደ ኢዜማ ያሉ የዜጋ ፓርቲዎች አብረው መስራት ግድ ይላልቸዋል። የፖለቲካ እንሰሶች ከሆኑ ማለት ነው።

አይ ይህ አይሆንም ፣ ፖለቲካ እንሻረክ ካሉ ደሞ አቢይ የተወሰኑ የመንግስት ስልጣኖች ለነዚህ ፓርቲዎን ሼር በማድረግ የራሱን የድጋፍና ፖለቲካ መሰረት ማስፋት አለበት ።

በጥቂት የፒፒ ድብቅ የጎሳ ባንዳዎች ላይ እስከ ቆመ ድረስ ነጋ ጠባ ሊያወርዱት መጥለፈ መንግስት እንደ ሚሞክሩ ሳይታለም የተፈታ ነው ....

ይቀጥላል ........



Last edited by Horus on 31 Jul 2020, 17:13, edited 1 time in total.


Guest1
Member
Posts: 1926
Joined: 28 Dec 2006, 01:02

Re: አቢይ አህመድ፤ የኢትዮጵያ ከማል አታቱርክ! በታማኝ ኢትዮጵያዊና በጎሳ ባንዳ መሃል ያለው ግዙፍ ትግል !!!

Post by Guest1 » 31 Jul 2020, 10:02

Horus
ኣታቱርክ?
ኢሃድጎች ኢትዮታጵያ ከመፈራረስ ያዳንን ነን ስለሚሉና በአንድነት ስላቆዩ የመጀመሪያው አታቱርክ ኢሃድግ ነው። አንዳንዶች እንደሚተቹት ኢትዮጵያን እኛ እናስተዳድራን፤ ኢሳያስ አንተ ኤርትራን ኣስተዳድር ብለው ለሁለት ከፍለው የራሳቸውን መንግስት ያቋቋሙ ከሆነ ሌላ ስም ይሰጣቸዋል። ኣቢይ በኢህ ኣድግ የተመሰረተችውን ኢትዮጵያ እንዳለች ለመቀጠል ስለፈለገ ሁለተኛው ኣታቱርክ ልንለው? እያስቀጠለ ብቻ ሳይሆን እያነገሰ ነው እንደሚባለው ከሆነ ደግሞ ሌላ ስም ይፈለግለት። በክልል እየሸነሸነም ቢሆን፤ ዳርድንበሯን እያስጠበቀ ከቀጠለ ከኢሃድግነት የተለየ ኣይደለም ነው። ኤርትራን ያስመለሰ ቀን ብቻ አታ ቱርክ ማእረግ ሊሰጠው ይችላል።
ኣታ ቱርክ ማን ነው?
የቱርኮች አባት፤ የኦቶማን ግዙፍ ግዛቶች ሲፈራርሱ የአሁኗ ቱርክ ዳርድንበሯን ኣስጠብቆ ያቆየ መሪ ነው። ኤርትራ ካስገነጠለ ብኋላ የቀረውን ያዳነው ኢህኣድግ ቢሆነው አገር ያተረፈና አገር ኣሳልፎ የሰጠን ለማመሳሰል መሞከር እንዴት ይቻላል? ኣቢይ ከኢህኣድግ የወረሰውን እንዳለ ሲያስቀጥል ስም መሽለም ኣይቻልም። ወይ ሁለቱም አታ ቱርኮች ናቸው ወይም ሌላ ስም ይሰጣቸው።

Horus
Senior Member+
Posts: 30668
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: አቢይ አህመድ፤ የኢትዮጵያ ከማል አታቱርክ! በታማኝ ኢትዮጵያዊና በጎሳ ባንዳ መሃል ያለው ግዙፍ ትግል !!!

Post by Horus » 31 Jul 2020, 14:37

Guest1

የተጻፈውን ሳታነብ ለምን ለመልስ ትቸኩላለህ? መልሰህ አንብበው? መለስ የከማል አታቱርክ ተቃራኒው ነበር ። ኢትዮጵያ የሚለውን ቃል መጠቀም የሚቀፈው የጎሳ ባንዳ መደብ ነበር ፤ እሱ በከፋፈላት ኢትዮጵያ ዛሬ ጂኖሳይድ የሚካሄድው ። ግዜህን ለምን ታባክናለህ ከኔ ጋር ማለት ነው?

Horus
Senior Member+
Posts: 30668
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: አቢይ አህመድ፤ የኢትዮጵያ ከማል አታቱርክ! በታማኝ ኢትዮጵያዊና በጎሳ ባንዳ መሃል ያለው ግዙፍ ትግል !!!

Post by Horus » 31 Jul 2020, 17:11

አቢይ አህመድ ፓርቲዎችን ሰብስቦ ያናገረው ለምንድን ነው? ብዙ የሚዲያ ሰዎች ያቢይ አላማ ምን እንደ ነበር አልያዙትም። ራሳቸው ፓርቲ መሪዎቹ የሱ አላማ ምን እንደ ሆነ አልገባቸውም። አቢይ ፓርቲዎቹን የጠራው ኦሮሞ ውስጥ ስለተደረገው ነገር ለመወያየት አይደለም፤ ያ ፖሊስና አቃቤ ሕግ በየግዜው መግለጫ ይሰጣሉ ። የስብሰባው አላማ ሁለት ናቸው ።

አንደኛውና ቀዳሚው በአባይ ግድብ ዙሪያ ሙሉ ብራቮና ድጋፍ ከፓርቲዎቹ በማግኘት የፖለቲካ ቤዙን አስፍቶ ከፍተኛ የገንዘብ ስብሰባ ዘመቻ ለማድረግ ነው። ይህ የሱ ቁጥር አንድ ትኩረቱ ስለሆነ ። ሰላምና ጸጥታ በሚመለከት እነዚህ ፓርቲዎች የሚፈይዱት ነገር የለም ። ያ እየሆነ ያለው በሰራዊቱ፣ ፖሊስና በስለላው ድርጅት ስለሆነ ።

ሁለተኛው አላማ የታሰሩ ፖለቲከኞችን ሕግ እና ሰርዓት ብሎም ወንጀል ጋር በማያያዝ ፓርቲ ድርጅቶችን ከታሰሩት ሰዎች ለመለየት (ፒፒ ወንጀለኞችንም ጨምሮ) እነዚህ ተፎካካሪዎች የሱን ጥርስ ማብቀል እንዲደግፉ ነው ። ያቢይ ሁለተኛ ቁልፍ ትኩረት የፖለቲካ ቤዙን ከጎሳ ባንዳዎች (ቆሻሻ ሌቦች ያላቸውን) አውጥቶ ኢትዮጵያዊ ወደ ሚለው የፖለቲካ ጎራ ለማዞር ብሎም ይህን አዝማሚያ ለመለካት ነው የሰበሰባቸው።
ባሁን ግዜ አቢይ ከጎሳ ባንዳው መደብም ከኢትዮጵያዊ መደብም ጋር ሊጣላ አይችልም፣ በቂ የፖሊቲካ ሶሺያል መቆሚያ ድጋፍ ይፈልጋል ። ይህ ነው ዋናው ነገር ። ይህ ሁሉ ሲሆን አቢይ ቀስ በቀስ ዲክታተር ሊሆን ይችላል ለሚሉ መልሱን ከላይ ብዬዋለሁ ። ያ የሚወሰነው የኢትዮጵያዊ ካምፕ ከሱ ጋር በሚያደርገው ድጋፍ፣ ክትትል፣ ቁጥጥር እና ተጸዕኖ ነው። አቢይን በኢትዮጵያ ፈረሰ እንዲጋልብ ማድረግ ማለት የሱን የስልጣን መሰረት መቆሚያ ኢትዮጵያዊነት እንዲሆን ማድረግ ነው። ይህ ነው ፖልቲካ ማለት!!

Wedi
Member+
Posts: 7959
Joined: 29 Jan 2020, 21:44

Re: አቢይ አህመድ፤ የኢትዮጵያ ከማል አታቱርክ? በታማኝ ኢትዮጵያዊና በጎሳ ባንዳ መሃል ያለው ግዙፍ ትግል !!!

Post by Wedi » 31 Jul 2020, 17:28

ወንድይራድ ሀይለገብርኤል

እንዄን ለመመረጥ ለመምረጥም መታገድ የሚገባቸው አያቶቻችን!!!

ሀሳቡን ለመግለፅ ከባድ ነው። ቢሆንም ልሞክር።
----

ትንሽ ቆየት ብሏል። የህግ ትምህርትቤት ውስጥ እያለው "Legal Analysis and Problem Solving" በተባለ አንድ ዩኒት ውስጥ የምርጫ ህግ ፍተሻ የተሰኘ ኢፒሶድ ነበር።

ግብሩ ወይንም ምርምሩ የምርጫ ህጉን ፈትሾ ሊሻሻሉ/ሊጣሉ/ሊጠቃለሉ ወይንም ሊታደጉ (amended /repealed /consolidated or revived) የሚገባቸው ህጉች ካሉ ዲያጎኖሲስ ሰርቶ ፕሮፖዛል ማቅረብ ነው።

የኔ ሪኮመንዴሽን የሚከተለው የምርጫ ማስፈፀሚያ ደንብ ላይ ያተኮረ ነበር። ደንቡ የዕድሜ ገደብ ተቀምጦለት amended ሊደረግ ይገባል ነው ያልኩት። የዕድሜ ገደቡም ከ 18 - 65 አመት ሊደረግ የተገባ ነው ነበር ያልኩት።

የፌደራል መንግስቱ የምርጫ ማስፈፀሚያ ህግ 1918 አንቀፅ 245 ቁጥር 1 እንዲህ ተመልክቷል ""ከ 18 አመት በላይ ለሆናቸው ዜጎች በሙሉ መምረጥ ግዴታ ነው it shall be the duty of ---- compulsory to all citizens over the age of 18 to enroll and vote""

መከራከሪያየን ያስቀመጥኩት ባጭሩ እንደሚከተለው ነበር፡ --

*** ዕውነታ አንድ: የሴቶች ዕድሜ ዘመን life expectancy በአማካኝ 84 አመት ሲሆን የወንዶቹ ደግሞ 80 አመት ነው። እስካሁን ድረስ 4250 ዜጎች መቶ አመት ደፍነዋል። 110 አመት ሞልቷቸውም እስካሁን ያላለፉ በርካታ ዜጎች አሉ። እንግዲህ መምረጥ የሚችሉትና መምረጥ ግዴታቸው የሆኑ እነዚህ ሁሉ አዛውንቶች ናቸው። ግዴታ ስለሆነ አብዛኛዎቹ የሚመርጡት አልጋ ላይ እንደተኙ ነው።

*** ዕውነታ ሁለት፡ ከ 24 ሚሊዮን የሀገሪቱ ጠቅላላ ህዝብ እድሜው 65 እና በላይ ያለው የሽማግሌና ጡረተኛ ቁጥር 30 በመቶ ነው።

*** ዕውነታ ሶስት፡ 16 ሚሊዮን ከሚሆነው ለመምረጥ የደረሰ Eligible to vote ማለትም 18 እና ከዚያ በላይ ከሆነው የህዝብ ቁጥር መካከል 50 በመቶ የሚሆነው ጡረተኛና የሽምግልና ዘመኑን በአዛውንቶች ማቆያ ስፍራ ተቀምጦ በአማካኝ በቀን እስከ 12 የደረሱ የተለያዩ መድሀኒቶችን በመውሰድ ቀኑን እየገፋ ያለ ነው።

ያቀረብኩት የማስተካከያ amendment ሀሳብ በከፊልና ባጭሩ፡ --

*የምርጫ ማስፈፀሚያ ህጉ 1918 s245 ተሻሽሎ የመራጭነት ግዴታው የዕድሜ ገደብ ሊጣልበት ይገባል። ገደቡም ከ 18 -65 ቢሆን መልካም ነው። 65 የጡረታ መውጫ ዕድሜ ነው።

*ሰው ጡረታ ከወጣ በሗላ ህይወቱን የሚገፋው ስራላይ በነበረበት ግዜ ባጠራቀመው የሱፐርአኑየሽን እና ከሰራተኛው ሀይል በግብር አግባብ በተሰበሰበ የመንግስት ፔንሽን ፈንድ ነው።

*ለጡረተኞች ነፃ ህክምና በፖለቲካል ፓርቲዥያን የማይናወጥ የዜጎች መብት በመሆኑ ጡረተኛው ከሰራተኛው ሀይል በሚሰበሰብ ግብር ተንቀላጦ መኖር አልበቃው ብሎ የወጣቱንና የሰራተኛውን ህይወት ሊያናጋ በሚችል የፖለቲካ ምርጫ ላይ እየተሳተፈ የወጣቱንና የሰራተኛ ሀይሉን እጣ ፋንታ ሊወስን አይገባም።

*ስለማይኖርበት የስራና የትምህርት ፖሊሲ ምርጫ ላይ መሳተፍ የለበትም። የወጣቱ የወደፊት ዕጣ ፋንታ የራሳቸውን ኑሮ አጣጥመው ባበቁ የመቶ አመት አዛውንቶችና ጡረተኞች political determination ሊሰጠው አይገባም። ዛሬ ላይ የጡረታ መውጫውን እድሜ ከፍ አድርገውታል።

እኒህንና ተያያዥነት ያላቸውን 27 ነጥቦች በማንሳት ደንቡ ሊሻሻል ይገባል የሚል ፕሮፖዛል ነበር ያቀረብኩት። ባቀረብኩት ፕሮፖዛል ቢገረሙም የወደዱት ግን አልመሰለኝም። የዲሞክራሲ ፅንሰሀሳብን ይንዳል የሚል ትችትም ሰጥተውበታል። ሊንድ ይችላል። የአንፃራዊነት ባህሪው የዚሁ መገለጫ ነው።

ለኢትዮጵያ ፖለቲካም መፍትሄ የምለው ይህንኑ ነው። የተከበሩ አባቶቻችን እነጋሽ በየነ ጴጥሮስ፡ አረጋዊ በርሄ፡ መራራ ጉዲና እንዃንስ ሊመረጡ ሊመርጡም ሊፈቀድላቸው አይገባም። they have had their time and chances አልተጠቀሙበትም። ለማያባራ መከራ ነው የዳረጉን። የሌላ አለም ሰዎች ናቸው። አካላቸው እንጅ አስተሳሰባቸው ከዚህ ትውልድ ጋር ቁርኝት የለውም። ሀገሪቱ አቅም ካላት ለነዚህ አዛውንቶች ማድረግ የምትችለው ሰብሰብ አድርጋ የዕድሜ ጠገብ ማዕከላት ውስጥ በማስገባት መጠወርና የቀን ክኒናቸውን ሳታጓድል ማቅረብ ነው።

ስለማይኖሩበት አለም የወጣቶቻችንና የሀገራችን የወደፊት እጣ ፋንታ ላይ ጭቃ እንዲያቦኩ ሊፈቀድላቸው የተገባ አይደለም። በአፄ ሀይለስላሴ ዘመን የደነቆረ ጀሮ በአብይ ዘመን ሊሰማ አይችልም። they all expired! ኢትዮጵያ የወጣቶች ሀገር ናት። በወጣቶች ፖለቲካዊ ተሳትፎ ልትገነባ የግድ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩን የገጠማቸው ፈተና ከባድ ነው። ከእኒህ old geared mentalities ጋር እንዴት ተሁኖ ነው መደመርስ መለወጥስ የሚቻለው?

እኒህ ሰዎች የመምረጥም የመመረጥም መብታቸው በሲቪል አክሽን ሊታይ ይገባል። ማህበረሰባዊና ሀገራዊ ደህንነት ከዲሞክራሲያዊ ፅንሰሀሳብ በላይ ነው።

ከባድ ነው!!!


Abere
Senior Member
Posts: 10894
Joined: 18 Jul 2019, 20:52

Re: አቢይ አህመድ፤ የኢትዮጵያ ከማል አታቱርክ? በታማኝ ኢትዮጵያዊና በጎሳ ባንዳ መሃል ያለው ግዙፍ ትግል !!!

Post by Abere » 31 Jul 2020, 17:40

ወዲ፣
በዕድሜ አግላይ Age discrimination ያለበት አይመስልህም? የዝቅተኛ ዕድሜ ወለል መወሰን ይቻላል ግን ጣራውን መወሰን ፍትሃዊ አይመስለኝም። በእርግጥ እንዳልከው የበየነ ጴጥሮስ እና የመራራ ጉዲና ነገር ስልችት የሚያደርግ ነው። መተዳደሪያ አድርገውት ነው። የእነርሱ ጥፋት አይመስለኝም - ወጣቱ እራሱ እነርሱን ለምን ይከተላል።

Horus
Senior Member+
Posts: 30668
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: አቢይ አህመድ፤ የኢትዮጵያ ከማል አታቱርክ? በታማኝ ኢትዮጵያዊና በጎሳ ባንዳ መሃል ያለው ግዙፍ ትግል !!!

Post by Horus » 31 Jul 2020, 21:44

አበረ፣

እርግጥ በወጣቱ ዘንድ የተረኛነት ችኮላና ይገባናል ስሜት አለ ። ትልቁ ችግር የሰዎቹ አካላዊ እድሜ ሳይሆን የሃሳባቸው እርጅና ነው። ልክ አቢይ እንዳለው የሁላቸውም ሃሳብ አብሮ ቢጨመቅ ከ3 ወይ አራት መሰራቲ ቲኦሪ አያልፍም። ችግሩ ሁልም አንዷን ወምበር ላይ ሊወጡ ያልማሉ ። ኢትዮጵያ ቢበዛ ከ5 ፓርቲዎች በላይ አያስፈልጋትም፤
አንድ የኢትዮጵያ ናሽናሊዝም ዙሪያ ሚያጠነጥን፣
አንድ ለቋንቋ፣ ባህል እዘተ ሚሙገት የዛሬ ብልጽግና አይነት፤
አንድ ሊብራል ዴሞክራሲ ዙሪያ፣
አንድ ሶሺያል ዴሞክራሲ ዙሪያ (ኢዜማ ማለት ነው)፣
አንድ ኢኮሎጂ ላይ ሚሰራ አረንጓዴ ፓርቲ ። በቃ
ይብዛ ከተባለና በቂ ማህበራዊ መሰረት ካለው ሕገ መንግሳትዊ የዘውድ ፓርትይ።
ይህ እንግዲ 6 ፓርቲዎች ማለት ነው ። በምድር ላይ ያለው ፖሲብል ሪያሊቲ እነበየነ ምናምን ባዶ ምናብ ይዘው ነው ወደ መቃብር እየወረዱ ያለው።

የጎሳ ፓርቲ ወይ ድርጅቶች ሁሉ ተሽረው የሲቺክ ማህበር መሆን አለባቸው ። እንሱ ላካባቢያቸው ጥቅም የሚሟገቱ ፕሬሸር ቡድን እንጂ መንግስት የሚመሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከቶም መሆን አለነበረባቸውም፣ በአንድ ዘመናዊ ህበረተሰብ ውስጥ !!


tlel
Member
Posts: 1559
Joined: 28 Dec 2019, 14:24

Re: አቢይ አህመድ፤ የኢትዮጵያ ከማል አታቱርክ? በታማኝ ኢትዮጵያዊና በጎሳ ባንዳ መሃል ያለው ግዙፍ ትግል !!!

Post by tlel » 02 Aug 2020, 02:14

ኣልገባኝም ኣንድ በጣም ኣደገኛ ነገር እየተከሰተ ነው። ህዝብ በሶሻል ሚዲያ ምክንያት እየተከፋፈለ ነው። በተለይ ኢትዮዽያዊ ነን የሚሉ ሁሉም በራሳቸው መልክ እንጂ ድሮ እንኳን የተለያየ ቀለም ያላት ኢትዮዽያ እንኳን ኣሁን እየቀነሰ ነው። ቆይ እነዚህ በኢትዮዽያ ስም የሚነግዱ ትግስት በማጣት ዶር ኣብይን ኣውርደው ማንን ሊተኩ ፈለጉ፧ ኣልገባኝም ነው እልም ያለ ጦርነት ኢትዮዽያን ለመከተት ነው። የት ነበሩ ሚዲያ ላይ ህዋሃት እያለ ኣንዳቸውም የሉም ነበር እንደ ሳምሶም ጋዜጠኛው ያለው መልኩን ቀይሮ ያሁኑ መንግስት ውስጥ ደሞ ለመግባትና ሸርነቱ እንዳይታወቅበት በየዘራቸው ውስጥ እየገቡ ትግላቸውን ቀይሰው እያመለጡ ነው ከህዋሃት ጋር ያላቸው ግነኙነት እነዳይታወቅ። ሌላው ደሞ፣ ዶር ኣብይን መጠርጠር ይሁን ግን ምርጫ ከሌለ እሱን መደገፍ ሰዉ ምብቱ ነው፣ እልቅ ከሱ ጋር እየሰሩ ኣገሩን ማስተካከል ተመራጭ ነው ኣለበለዚያ ኣብይ እንደዚህ ኣለም ኣብይ ዘጋኝ እያሉ ወዘተ መቃወም እውነትም ለኢትዮዽያ ብለው ኣይደለም የሚታገሉት ለራሳቸው ስሜት ለሟሟላት እንጂ ወይም በሚስጥር በዘራቸው ተደብቀው የሚያራምዱት ትግል ነው። ይህ ሚዲያ ላይ የኢትዮዽያን ህዝብ እየከፋፈለው ነው በፊት ኣንድ ሆኖ ህዋሃትን ሲታገል የነበረው። ለምሳሌ ዳዊት ኣራያ የሚባል ሶሻል ሚዲያ ላይ ኣሁን ስለ ህዋህት መናገር ኣቁሞ ኣብይ ላይ ውርጅብኝ ጀምሯል። ኣላማውም ምን እንደሆነ ኣይታወቅም፣ እንደዚሁ እነ መስፍን ቶሎሳ የሚባለውን ለምን ስለ ኢትዮዽያ ተናገርከው ብሎ ሲዘልፈው ነበር ኣሁን ደሞ ኮር ዳዊት የሚባለውን ሚዲያ ላይ እየዘለፈ ይገኛል። በኢትዮጵያ ስም ስር ተደብቆ ይህ ሰው ለኢትዮዽያ የሚታገሉትን ለምን እንደኔ ኣልሆናችሁም ብሎ እያጠቃና ህዝብን እየከፋፈለ ነው።

ህዋሃት በምርጫ ሊሸነፍ ሲል ለኢትዮዽያውያን ስልጣኑን ኣልሰጥም ብሎ መለስ ዘናዊ ወደ ሚነሶታ መቶ ለኦነጎች ኑ ህዋሃት ከስልጣን ሊወርድ ስለሆነ ስልጣኑን ተረከቡን ኣላቸው። ሳይሆን ቀረ ህዋህት ስልጣኑን በግድ እንደገና ተቆጣጠረው። ይመስለኛል ዛሬ ደሞ ፊቱን ያዞረው ከኣንዳንድ ፅንፈኛ ኣማራ ነኝ የሚለውን እንደነ ልደቱን፣ ሳምሶንን ልክ እንደ ኦነግ ስልጣን ለኣማራ ነው ለማለት ያቃታው ይመስላል። ኢቲ ፫፮ 0 ኣላማቸው ምንድን ነው፣ ህዋሃት ወይም ህዋሃትን ሲረዳ የነበረው የውጭ ሃይል ቃል ኪዳን የገባላቸው ይመስላል። እርግጥ በትክክል ነገር የብልፅግናን ፓርቲ መተቸት ማስተካከል ኣለበት ኣለበለዚያ ከዛ ውጪ ካላቸው ኣላማ፣ ኣገሪቱን በደም ለማጉረፍ ማዘጋጀት ነው። የዳዊት ኣሯያው በከፊል እውነት ሀገ መንግስቱ መቀየር መስተካከል ይኖርበታል እውነቱን ነው ግን ህፃን ልጅ ይመስል ሁኔታው ያገሪቱን ሳያይ እኔ ያልኩት ለምን ኣይሆንም በማለት ሁሉንም መዝለፍ ተገቢ ኣይደለም ሁሉም ለኢትዮዽያ መታገል በራሱ መንገድ መብቱ ነው። ይህ ልጅ ዞሮ ዞሮ እራሱ ዘር ውስጥ ኣይበለው እንጂ በእጅ ኣዙር ስለ ሀገ መንግስት እንጂ ህዋሃትን እንኳን ስማቸውን ኣያነሳም። ያጠራጠራል. people are being divided!! stop it!

Horus
Senior Member+
Posts: 30668
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: አቢይ አህመድ፤ የኢትዮጵያ ከማል አታቱርክ? በታማኝ ኢትዮጵያዊና በጎሳ ባንዳ መሃል ያለው ግዙፍ ትግል !!!

Post by Horus » 02 Aug 2020, 04:15

tlel

ብዙ ነገሮች አንስተሃል፤ ባንዱ ላይ ብቻ ሃሳብ ልስጥ። አንድ ሚዲያ፣ የኮሚኒኬሽን መሳሪያ ማንም ይሁን ማ በሆነው የመገናኛ ዜዴና አይነት አንድ ነገር ሲያደርግ የሚገፉት ወይም የሚነዱት ፍላጎቶች ምንድን ናቸው ሲባል ያሉት ሞቲቮች አራት ናቸው ። እነሱም የሚከተሉት ናቸው ።

አንድ፣ ክሚኒኬት ስናደርግ አላማችን ሌሎችን (ሰሚ ታዳሚን) ለማዝናናት፣ ለማጫወት፣ ለማስደሰት ነው። ይህ የኢንተርቴይንመንት ስራ ወይም አላማ ይባላ። ግባችህን ሰዎችን ማስደሰት ነው።

ሁለት፣ ኮሚኒኬት ስናደርግ አላማችን ሌሎችን (ሰሚ ታዳሚን) ማስረዳት፣ ማስታወቅ፣ መረጃ መስጠት፣ ኢንፎርም ማድረግ ነው ። ጥያቄው ስለምንድን ነው የሚያስረዱት፣ የሚያስታውቁት፣ ኢንፎርም የሚያደርጉት የሚለው የጋዜጠኞቹን አቋምና አመለካከት ይነግረናል ። ስለዚህ አንድ የሚዲያ ሰው የሚያቀርበውን መረጃ የሚመርጠው በሱ አመለካከት መሰረት ነው።

ሶስት፣ ኮሚኒኬት ስናደርግ አላማችን ሌሎችህን ማስተማር ነው። ስለዚህ ማናኛውም የዜና ሚዲያ ስንከታተል ያ ሚዲየም ምን እንደ ሚያስተምር መጠየቅና ማወቅ አለብን ። አንድ ትምህርትም ቢሆን ትምህርቱ፣ እውቀቱ ስለምንድን ነው ብለን መጠየቅ አለብን? ሚዲያው የሚሰጠውን ትህምርት ካልተስማማን ከሚዲያው ጋር የዕውቀት ቅራኔ አለን ማለት ነው። በአንድ ዴሞክራሲ ውስጥ እውቀት ክፍት መሆን አለበት ። የሚዲያ ስራ ሕዝብን ስለሁሉም ነገር ማስተማር ነው ።

አራተኛ፣ ኮሚኒኬት ስናደርግ አላማችን ሌሎችን ለማነቃቃት፣ ለማነሳሳት፣ ለመቀስቀስ፣ ለመግፋት፣ ሞቲቬት አጂቴት ለማድረግ ነው። ማለትም እኛ ወደ ምናምንበት፣ ምንወደው አቋም፣ አላማ፣ ቦታ፣ አቅጣጫ ሌሎችን መሳብ፣ መለወጥ ነው ።

የኮሚኒኬሽን አላማ ሳይንሳዊ መለክያ እነዚህ 4 ግቦች ናቸው። በዚህ መለኪያ መሰረት ኢትዮ360 (1) ኢንፎርም የሚያደግ አገልግሎት ይሰጣሉ፤ (2) በማስተርማር እውቀት ይሰጣሉ፤ (3) ሞቲቬት በማድረግ ሌሎችን ወደነሱ አስተያየት ለመውሰድ ያበረታታሉ ።

በዚህ መሰረት አራት ወይም አምስቱም ግለሰቦች የራሳቸው እምነት፣ አቋም፣ እና ግብ አላቸው ። ይህን እያንዳንችን ልብ ብለን የምንወደውን መውሰድ ፣ የጠላነውን መተው የኛ ሃላፊነት ነው። ስለዚህ ነው እኔ የማተኩረው በሚያቀርቡት ሃሳብ ላይ የሆነው። በኔ ግምት ኢትዮ360 የአንድ ፓርቲ ፕሮግራም የሚያራምድ ድምጽ አይደለም ። ሁልግዜም ያቢይ ደጋፊ አይደለም፤ ሁልግዜም ያቢይ ተቃዋሚ አይደለም ፤ እስከ ዛሬ ባየሁት ማለት ነው ።

Guest1
Member
Posts: 1926
Joined: 28 Dec 2006, 01:02

Re: አቢይ አህመድ፤ የኢትዮጵያ ከማል አታቱርክ? በታማኝ ኢትዮጵያዊና በጎሳ ባንዳ መሃል ያለው ግዙፍ ትግል !!!

Post by Guest1 » 02 Aug 2020, 05:52

ኢትዮ 360
አንዳንዴ ተንኮለኛና አምታቺ ይመስላል። በማያግባባና ከጊዜው ጋር የማይሄድ ለምሳሌ ኮንስቲትዩሽን መሰረዝ ላይ ያተኩራሉ። በተደጋጋሚ ስህተቶች እንዳልሰራ ኣጋነው እስክንድርን መልኣክ ለማድረግ ይቃጣቸዋል።
ኣንዳንዴም መካድ የማይቻለው ግሩም የሆነ ትንተና ያቀርባሉ።
ኣቋም የለሽ የሚያሰኝ ባህሪይ ኣለው ቢባል ስህተት ኣይሆንም።

Post Reply