. BTW: THIS WAS IN 1907.
-
- Senior Member+
- Posts: 33293
- Joined: 26 Feb 2016, 13:04
Photo Of: Atse Menelik Was Z 1st African Leader 2 Drive A Car @ Z Same Time Agame Yohanes Walked Bare-feet!!!WEEY GUUD!!
Last edited by tarik on 30 Jul 2020, 16:30, edited 1 time in total.
-
- Member+
- Posts: 7993
- Joined: 29 Jan 2020, 21:44
Re: Photo Of: Atse Menelik Was Z 1st African Leader 2 Drive A Car @ Z Same Time Agame Yohanes Walked Bare-feet!!!WEEY GU
ዳግማዊ አጼ ምኒልክና ኢትዮጵያን ዘመናዊ የማድረግ ሕልም !
ዘመናዊ የአስተዳደር ተቋም የካቢኔት ሹመትን የጀመሩት ምኒልክ ናቸው ። በዚያን ግዜ ድርጊታቸውን የሚነቅፉ ተቃዋሚዎች ቢበዙባቸውም ራሳቸው እንደ ተራው ሰው ወርደው ላይ ታች በማለት ወፍጮ እያስፈጩ ፣ መኪና እየነዱ ፣ በስልክ እያወሩና የመሳሰሉትን እያደረጉ ህዝባቸው እንዲለምድ ብዙ ደክመዋል ።
ዳግማዊ አጼ ምኒልክ ታጋሽ አስተዳደር አዋቂ ሕዝብን በብቃትና ዘመናዊ በሆነ መልኩ ለማስተዳደር የሚችሉ መሆናቸው ይነገራል ፤ በተጨማሪም እርቅ በማድረግ ፣ በመደራደርና ችግሮችን በመፍታት ያምናሉ ። ሁልጊዜም ተዋግተው ድል ካደረጓቸው ጋር እርቅ አድርገው ተስማምተው ከተለያዩ ሹማምንቶች ጋር በአንድነት ኖረዋል ። ዳግማዊ አጼ ምኒልክ የግል ንብረት በመሰብሰብ የሚያምኑ መሪ አልነበሩም ። በዘመናቸው ከቤተመንግሥት ውጭ በስማቸው የተመዘገበ ርስት ስለሌላቸው ለልጆቻቸው ያወረሱት ምንም ንብረት አልነበረም ። ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ሲለፉና ሲደክሙ የነበረው ግን ኢትዮጵያ በባእድ ወራሪዎች እንዳትደፈርና ከውጭው ዓለም እኩል በዘመናዊነትና በቴክኖሎጂ እንድትጓዝ ነበር ።
ዳግማዊ አጼ ምኒልክ በንግስና ዘመናቸው ኢትዮጵያን ዘመናዊ ለማድረግ ከነበራቸው ሕልምና ከተገበሯቸው ብሔራዊ ተግባራት በጥቂቱ እነሆ : –
☞ ስልክ ውጭ በተሰራ በ12 አመቱ አዚህ አስመጡ በ 1882
☞ ፖስታ ቤት በመክፈት በ 1896
☞ የሕትመት መሣሪያ ማስመጣት በ 1898
☞ የጥይት ፋብሪካ ማቋቋም በ 1899
☞ የማዕድን ፍለጋ ፕሮጀክት በ 1894
☞ የትራንስፖርትና የመገናኛ አውታሮችን ማቋቋም ( የባቡር መሥመር ዝርጋታ ከጅቡቲ – አዲስ አበባ) በ 1893
☞ ዘመናዊ ገንዘቦችን አስቀርጾ ማውጣትና ባንኮችን መክፈት በ 1898
☞ ገንዘብ መቅረጫ ማሽን አስመጥተው ሥራ ላይ ማዋል
☞ የክትባት መድሐኒት
☞ የኤሌትሪክ መብራት በመዘርጋት በ 1889
☞ የመንገድ የድልድይና የሕንፃ ሥራዎች ግንባታ በ 1896
☞ የሸክላ ፋብሪካ ማቋቋም
☞ ቶሎ የሚደርስ ልዩ የዛፍ ዘር አስመጥቶ መትከል በ 1886
☞ ዘመናዊ የከብት ማዳቀል እርባታ ሥራን ማስጀመር
☞ የሕክምና ተቋም ዘመናዊውን መድሃኒት አቀነባብሮ መጠቀም በ 1889
☞ ሆስፒታል በመጀመር በ 1890
☞ መድሃኒት መሸጫ ሱቅ ( pharmacy ) በመክፈት በ 1904
☞ የጽሕፈት መኪና በማስመጣት በ 1887
☞ ሲኒማ በመክፈት በ 1889
☞ የሙዚቃ ትምህርት ቤት በመክፈት በ 1887
☞ የመጠጥ ውሃ ቧንቧ ዝርጋታንና የጉድጓድ ውሃዎች ማደራጀት በ 1886
☞ የመጀመርያውን ጋዜጣ ” አእምሮ እና ጎህ ” በማሳተም በ1900
☞ የታርጋ ቁጥሯ D3130 የሆነች አውቶሞቢል በማስመጣትና ራሳቸው በመንዳት በ 1900
☞ ዘመናዊ ሆቴል ማቋቋም በ 1898
☞ የዲኘሎማቲክ ግንኙነትን በአቻነት ደረጃ አጠናክሮ መቀጠል
☞ የንግድ ግንኙነት ( ከውጭ አገሮች ጋር )
☞ የወሰን ክልል ስምምነት መፈረም
☞ በቂ ሕክምና ባልተገኘበት አጋጣሚ ማንም ሠው ታሞ ሲዳከም 48 ሠአት ሳይሆነው ሞተ ተብሎ በችኮላ እንደይገነዝ የሚያደርግ ደንብ አውጥቶ በሥራ ላይ ማዋል
☞ ባርነትን ማውገዝ እና በሕግ መከልከል
☞ በእየሩሳሌም ገዳም የኢትዮጵያ ይዞታ የነበረውን አርመን ፅርዓውያንና ግብፃውያን ስለአጣበቡት ከቱርክ ንጉሥ ከሡልጣን አብዱል ሂሚድሃን ጋር መልእክቶችን ተላልከው የአባቶችን ይዞታ ማስከበርና ማስፋፋት
☞ ለአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያውን የሠፈራ ማስተር ፕላንና የቦታ አስተዳደር ደንብ ማውጣት
☞ የድንጋይ ከሠል ማዕድንን ማግኘትና ወዘተ ….ከብዙ ጥቂቶቹ ናቸው ።
ምኒልክ ተወልዶ ባያነሳ ጋሻ
ግብሩ እንቁላል ነበር ይህን ግዜ አበሻ
በሰራው ወጨፎ ባመጣው እርሳስ
ተፈጠመ ጣልያን አበሻ እንዳይደርስ
ምኒልክ ተጉዞ የምትጠይቁኝ
ፊትም አላለፈ ኋላም አይገኝ ።
ታላቅ ክብር ለእምዬ ምኒልክ ይሁን !
ዋቢ መጽሐፍት : – ” አጤ ምኒልከ ” በጳውሎስ ኞኞና ከነጋድራስ ገብረሕይወት ባይከዳኝ ስራዎች
ዘመናዊ የአስተዳደር ተቋም የካቢኔት ሹመትን የጀመሩት ምኒልክ ናቸው ። በዚያን ግዜ ድርጊታቸውን የሚነቅፉ ተቃዋሚዎች ቢበዙባቸውም ራሳቸው እንደ ተራው ሰው ወርደው ላይ ታች በማለት ወፍጮ እያስፈጩ ፣ መኪና እየነዱ ፣ በስልክ እያወሩና የመሳሰሉትን እያደረጉ ህዝባቸው እንዲለምድ ብዙ ደክመዋል ።
ዳግማዊ አጼ ምኒልክ ታጋሽ አስተዳደር አዋቂ ሕዝብን በብቃትና ዘመናዊ በሆነ መልኩ ለማስተዳደር የሚችሉ መሆናቸው ይነገራል ፤ በተጨማሪም እርቅ በማድረግ ፣ በመደራደርና ችግሮችን በመፍታት ያምናሉ ። ሁልጊዜም ተዋግተው ድል ካደረጓቸው ጋር እርቅ አድርገው ተስማምተው ከተለያዩ ሹማምንቶች ጋር በአንድነት ኖረዋል ። ዳግማዊ አጼ ምኒልክ የግል ንብረት በመሰብሰብ የሚያምኑ መሪ አልነበሩም ። በዘመናቸው ከቤተመንግሥት ውጭ በስማቸው የተመዘገበ ርስት ስለሌላቸው ለልጆቻቸው ያወረሱት ምንም ንብረት አልነበረም ። ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ሲለፉና ሲደክሙ የነበረው ግን ኢትዮጵያ በባእድ ወራሪዎች እንዳትደፈርና ከውጭው ዓለም እኩል በዘመናዊነትና በቴክኖሎጂ እንድትጓዝ ነበር ።
ዳግማዊ አጼ ምኒልክ በንግስና ዘመናቸው ኢትዮጵያን ዘመናዊ ለማድረግ ከነበራቸው ሕልምና ከተገበሯቸው ብሔራዊ ተግባራት በጥቂቱ እነሆ : –
☞ ስልክ ውጭ በተሰራ በ12 አመቱ አዚህ አስመጡ በ 1882
☞ ፖስታ ቤት በመክፈት በ 1896
☞ የሕትመት መሣሪያ ማስመጣት በ 1898
☞ የጥይት ፋብሪካ ማቋቋም በ 1899
☞ የማዕድን ፍለጋ ፕሮጀክት በ 1894
☞ የትራንስፖርትና የመገናኛ አውታሮችን ማቋቋም ( የባቡር መሥመር ዝርጋታ ከጅቡቲ – አዲስ አበባ) በ 1893
☞ ዘመናዊ ገንዘቦችን አስቀርጾ ማውጣትና ባንኮችን መክፈት በ 1898
☞ ገንዘብ መቅረጫ ማሽን አስመጥተው ሥራ ላይ ማዋል
☞ የክትባት መድሐኒት
☞ የኤሌትሪክ መብራት በመዘርጋት በ 1889
☞ የመንገድ የድልድይና የሕንፃ ሥራዎች ግንባታ በ 1896
☞ የሸክላ ፋብሪካ ማቋቋም
☞ ቶሎ የሚደርስ ልዩ የዛፍ ዘር አስመጥቶ መትከል በ 1886
☞ ዘመናዊ የከብት ማዳቀል እርባታ ሥራን ማስጀመር
☞ የሕክምና ተቋም ዘመናዊውን መድሃኒት አቀነባብሮ መጠቀም በ 1889
☞ ሆስፒታል በመጀመር በ 1890
☞ መድሃኒት መሸጫ ሱቅ ( pharmacy ) በመክፈት በ 1904
☞ የጽሕፈት መኪና በማስመጣት በ 1887
☞ ሲኒማ በመክፈት በ 1889
☞ የሙዚቃ ትምህርት ቤት በመክፈት በ 1887
☞ የመጠጥ ውሃ ቧንቧ ዝርጋታንና የጉድጓድ ውሃዎች ማደራጀት በ 1886
☞ የመጀመርያውን ጋዜጣ ” አእምሮ እና ጎህ ” በማሳተም በ1900
☞ የታርጋ ቁጥሯ D3130 የሆነች አውቶሞቢል በማስመጣትና ራሳቸው በመንዳት በ 1900
☞ ዘመናዊ ሆቴል ማቋቋም በ 1898
☞ የዲኘሎማቲክ ግንኙነትን በአቻነት ደረጃ አጠናክሮ መቀጠል
☞ የንግድ ግንኙነት ( ከውጭ አገሮች ጋር )
☞ የወሰን ክልል ስምምነት መፈረም
☞ በቂ ሕክምና ባልተገኘበት አጋጣሚ ማንም ሠው ታሞ ሲዳከም 48 ሠአት ሳይሆነው ሞተ ተብሎ በችኮላ እንደይገነዝ የሚያደርግ ደንብ አውጥቶ በሥራ ላይ ማዋል
☞ ባርነትን ማውገዝ እና በሕግ መከልከል
☞ በእየሩሳሌም ገዳም የኢትዮጵያ ይዞታ የነበረውን አርመን ፅርዓውያንና ግብፃውያን ስለአጣበቡት ከቱርክ ንጉሥ ከሡልጣን አብዱል ሂሚድሃን ጋር መልእክቶችን ተላልከው የአባቶችን ይዞታ ማስከበርና ማስፋፋት
☞ ለአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያውን የሠፈራ ማስተር ፕላንና የቦታ አስተዳደር ደንብ ማውጣት
☞ የድንጋይ ከሠል ማዕድንን ማግኘትና ወዘተ ….ከብዙ ጥቂቶቹ ናቸው ።
ምኒልክ ተወልዶ ባያነሳ ጋሻ
ግብሩ እንቁላል ነበር ይህን ግዜ አበሻ
በሰራው ወጨፎ ባመጣው እርሳስ
ተፈጠመ ጣልያን አበሻ እንዳይደርስ
ምኒልክ ተጉዞ የምትጠይቁኝ
ፊትም አላለፈ ኋላም አይገኝ ።
ታላቅ ክብር ለእምዬ ምኒልክ ይሁን !
ዋቢ መጽሐፍት : – ” አጤ ምኒልከ ” በጳውሎስ ኞኞና ከነጋድራስ ገብረሕይወት ባይከዳኝ ስራዎች
-
- Member+
- Posts: 7993
- Joined: 29 Jan 2020, 21:44
Re: Photo Of: Atse Menelik Was Z 1st African Leader 2 Drive A Car @ Z Same Time Agame Yohanes Walked Bare-feet!!!WEEY GU
King Tewodros II.’s Sebastopol cannon
-
- Member
- Posts: 627
- Joined: 16 Jun 2013, 16:34
Re: Photo Of: Atse Menelik Was Z 1st African Leader 2 Drive A Car @ Z Same Time Agame Yohanes Walked Bare-feet!!!WEEY GU
ትክክል እኒህ ናቸው ታላቁ ምኒልክ::
በዓለም ታሪክ የተቀዳጁት ትልቅ ስፍራ ንቅንቅ የማይለው እምዬ ምኒልክ
ምድረ ባንዳ የፈለገውን ቢቀባጥር ቢወራጭ የእምዬ ተግባርና ክብር ስንዝር ያህል አይቀንስም
በዓለም ታሪክ የተቀዳጁት ትልቅ ስፍራ ንቅንቅ የማይለው እምዬ ምኒልክ
ምድረ ባንዳ የፈለገውን ቢቀባጥር ቢወራጭ የእምዬ ተግባርና ክብር ስንዝር ያህል አይቀንስም
-
- Member
- Posts: 4080
- Joined: 15 Jun 2018, 17:40
Re: Photo Of: Atse Menelik Was Z 1st African Leader 2 Drive A Car @ Z Same Time Agame Yohanes Walked Bare-feet!!!WEEY GU
King Minilik was one of a kind. He had done more for the country than all previous regimes combined. Great respect!!