Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Horus
Senior Member+
Posts: 30652
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by Horus » 19 Jul 2020, 22:14

እኔ እዚህ ፎረም ላይ ብዙ ግዜ በዳኛቸው ላይ የምለውን ብያለሁ፤ ስለማውቀና የሱን ማነትነት ምንም ሰለማያስገርመኝ ። ዳኛቸው ማለት ጋኖቹ ባለቁበት፣ ጋንኖች በሌሉበት አገር ስሙ የገነነ ምንጀት ነው ። ዛሬ ራሱን የዘውድ አገዛዝ ደጋፊ ነኝ ብሎ ፈርጇል። እኛ በወጣትነት ዘመን ኢፖለቲካዊ ጆሊ ጃክ ከተማሪ ንቅናቄ የተባረረ አባ ዝሙት ሴት አሳዳጅ ጸረ ፖለቲካ የነበረ ሰካራም ነው ። ግዙፋኑ የዘመኑ ትውልዶች ምደር ሰማይ ያናወጠ አብዮት ሲያነቃንቁ እና መስዋዕት ሲሆኑ የፊዩዳል ሴቶች ቀሚስ ስር እድሜውን የፈጀ የነጋዴ ልጅ ነው ። ከዚያም በሲጃራና ዉስኪ ከመሞቱ ቀድም በቤተሰቡ ዎያኔ አሽከርነት በዘመዱ ሌላው ሰካራም እንድሪያስ እሸቴ ዩኒቨርሲቲ ስራ ተስጥቶት ዛሬ ስሙን በደንብ የማይጽፍ የኮሌጅ ምሩቆችና የዘር ፖለቲካ ጥንቆላ አራጋቢ ትውልድ ጠፍጣፊ ነው ዳኛቸው ማለት ። ዛሬም ቢሆን የድምጽ ማጉሊያ በገኘ ቁጥር ሺ ግዜ ቢቀባጥር አንድ ጋዜጣ አንባቢ ወጣት ከሚያውቀው በላይ ስለፖለቲካ አያቅም፤ አወቀ ቢባል ድሮ የነበብናቸውን የመዕራብ ደራሲያን እንደ ፓሮት ወፍ ከመጥቀስ አያልፍም ። በዚህ እድሜውና ዘመን ልክ የተማሪ ማህበር ውስጥ እነደርግ እንደ ነበረው ፋክት እና ጥልቀት አልባ የሆነ ስሚታዊ ኢማቹር ፖለሚክስ እና ብሽሽቅ እንደ ፍልስፍና በማያውቁት ወጣቶች ዘንድ አግንኖ የሚኮፈስ የመሸታ ቤት ሊቅ ማለት እሱ ነው። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዛሬ 50 የሚያቁት እና ቦስተን ከተማ ለረጅም ዘመን የሚያውቁት ምስክር ናቸው ።

Ethio360ች ሁል ግዜ ትክክል ናቸው ማለቴ አይደለም ። እኔ የምለው ዳኛቸው አሰፋ ካድርባይ ምሁርነትም ያነሰ ዴማጎግና ኢፖለቲካዊ የመሸታ ቤት ታዋቂ ተራቢ ነው ። በእነ ኤርሚያ እና ሃብታሙ ሚዛን የሚነጽጸር አንጎል አይደለም ። እነሱም ራሳቸውን ከሱ ጋር ማወዳደራቸው ስህተት ነው፤ ራሳቸውን ነው ዝቅ የሚያደርጉት ።

Last edited by Horus on 19 Jul 2020, 23:10, edited 2 times in total.

Wedi
Member+
Posts: 7959
Joined: 29 Jan 2020, 21:44

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by Wedi » 19 Jul 2020, 22:28

Horus ይህ ሰው በጣም አሳፋሪ የሆነ ሰው ነው፡፡ ከአሁን በፊት የገነት ዘውዴ ወንድም ነስ ሲባል ስለሰማኹ ሰውየው የሚረባ ነገር አይደለም ብዬ ገምቸ ነበር፡፡ ዛሬ እነ ኤርምያስ ሲተነትኑት ሥማ ለካ ቤተሰቦቹና ዘመዶችቱ በሙሉ ተብ አዴ ከፍተኛ ባልስልታናት የነበሩ መሆኑን ነው የተገነሰብኩት፡፡ በተልይ በተልይ የዳዊት ዮሃንስ "ወንድም" ነው ሲሉን በጣም ነው የገረመኘ፡፡ ዳዊት ዮሃስን ማለት ከወያኔ በፊት በአሜሪካ ይኖር የነበርና የሆነ ሰካራም ሰው ነበር፡፡ ከዚያ መለስ ዜናው ከአሜሪካ ወስዶ የወያኔ አፈ ጉባኤ አድርጎት የኢትዮጵያን ህዝብ የወያኔ ተላላኪ ሆነ ሲያስጨፈጭፍ የነበረ ሰው ነው፡፡ ባጠቃላይ ገነት ዘዴን ጨምሮ ቁጥራቸው ወደ 6 የሚጠጉ የዶር ዳኛቸው ዘመዶች እና ቤተሰቦች በወያኔ ጊዘ በሚንስትርነት እና በከፍተኛ ቦታዎች ወያኔን ሲገለጉ ነበር፡፡

በጣም የገረመኝ ደግሞ ሰውየው አንተ ክድሮ ጀምሮ የምታውቀ አድርባይ የሆነ ሰው መሆኑን ስታረጋግጥ በጣም ነው የገረመኝ።

Horus
Senior Member+
Posts: 30652
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by Horus » 19 Jul 2020, 23:04

Wedi wrote:
19 Jul 2020, 22:28
Horus ይህ ሰው በጣም አሳፋሪ የሆነ ሰው ነው፡፡ ከአሁን በፊት የገነት ዘውዴ ወንድም ነስ ሲባል ስለሰማኹ ሰውየው የሚረባ ነገር አይደለም ብዬ ገምቸ ነበር፡፡ ዛሬ እነ ኤርምያስ ሲተነትኑት ሥማ ለካ ቤተሰቦቹና ዘመዶችቱ በሙሉ ተብ አዴ ከፍተኛ ባልስልታናት የነበሩ መሆኑን ነው የተገነሰብኩት፡፡ በተልይ በተልይ የዳዊት ዮሃንስ "ወንድም" ነው ሲሉን በጣም ነው የገረመኘ፡፡ ዳዊት ዮሃስን ማለት ከወያኔ በፊት በአሜሪካ ይኖር የነበርና የሆነ ሰካራም ሰው ነበር፡፡ ከዚያ መለስ ዜናው ከአሜሪካ ወስዶ የወያኔ አፈ ጉባኤ አድርጎት የኢትዮጵያን ህዝብ የወያኔ ተላላኪ ሆነ ሲያስጨፈጭፍ የነበረ ሰው ነው፡፡ ባጠቃላይ ገነት ዘዴን ጨምሮ ቁጥራቸው ወደ 6 የሚጠጉ የዶር ዳኛቸው ዘመዶች እና ቤተሰቦች በወያኔ ጊዘ በሚንስትርነት እና በከፍተኛ ቦታዎች ወያኔን ሲገለጉ ነበር፡፡

በጣም የገረመኝ ደግሞ ሰውየው አንተ ክድሮ ጀምሮ የምታውቀ አድርባይ የሆነ ሰው መሆኑን ስታረጋግጥ በጣም ነው የገረመኝ።
በትክክል፣ እኛ ሁለተኛ ደርጃ ሆነን ሰልፍ ስንወጣ እነሱ (ወንድሞቹ፣ በመኪና አደጋ የሞተች እህቱ) ከግቢ እንዳይወጡ በር ይዘጋባቸውና አጥር ላይ ሆነው ያዩን ነበር ። አንድ አመት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሳይቸርስ ወደ ቦስተን ሄደ ። እዚያ ሁለት አመት እንኳ ሳይሆነው ነው፣ ካብዮቱ በፊት በጆሊ ጃክነት ከተማሪ ንቅናቄ የተባረረው ። ከዚያም ይዎያኔ ደጋፊ እስከ ሆነ ድረስ በአንድም የዘመኑ ፓርቲዎች (ኢሃአፓ ሚኤሶ፣ ወዘተ) ደጅ ዝር አያቅም ። ዉስኪ፣ ሲጃራና ሴት ይዞ መንም ከኢትዮያ ጋር የማይገናኝ ክንቲኔታል ፊሎሶፊ ላይ ሮማንቲሳይዝ ሲያደር የኖረ ሰው ዛሬ በፖለቲካ ትግል ካደጉት እነኤርሚያስ ጋር ማሳተያየት ቀልድ ነው። እሱ የተሳሳተ ጎራ ወስጥ ነው እየገባ ያለው።

ታንሽ ወንድሙ ገነነው አሰፋ የበረከት ስሞን ንግግር ጸሃፊ ሆኖ ነበር የጀመረው ኋላ የሆነ ዎያነ ቃል አቀባይ አረጉት ። ብቻ መላ ቤተ ሰቡ የዎያኔ አሽከሮች ናቸው ።

gagi
Member
Posts: 618
Joined: 16 Jun 2013, 16:34

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by gagi » 19 Jul 2020, 23:11

በቃ ድሮ እንዲህ ነበር በሚል የአሁን አመለካከቶቹን ማጣጣል። ድሮ ሰካራም፤ ሴት አሳዳጅ ነበር፤ እናንተ ሪቮ ስትሆኑ እርሱ ጆሊነትን መርጦ ሊሆን ይችላል። ቁም ነገሩ አሁን ነገሮችን እንዴት ይተነትናል፤ ትንተናዎቹ የአገርን ሁኔታ በማሻሻል ፋይዳ አላቸው ወይ፤ ይህ ነው ቁም ነገሩ። አንተ የምትደግፈውን ሚዲያ ስለተቸብህ ይህን ሁሉ ጥላሸት መቀባት ምን አመጣው! አንተን ማን ያውቅሃል? እዚህ አዋቂ ለመምሰል ከምታደርገው መፍጨርጨር ውጪ አላውቅህም። ዐላማህ ምንድነው? የዳኛቸውን ስም በማጥፋት ግብህ ምንድነው። ኢትዮ 360 የሚባለውን የዘባራቂዎች ሚዲያ መከላከል ነው? ዳኛቸውን ዝቅ በማድረግ ራስህን ከፍ ማድረግ እችላለሁ በሚል እምነት ነው? እዚህ የዘከዘክኸው እውነት ቢሆን እንኳን ለዚህ ፎረም ሰዎች ማቅረቡ ፋይዳው ምንድነው? በሽተኛ!!

Horus
Senior Member+
Posts: 30652
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by Horus » 19 Jul 2020, 23:42

ጋጊ
እኔ የዳኛቸውን ስም ለማጥፋት አላማም ፍላጎትም የለኝም ። ዳኛቸው የሚጠፋ ስም የለውም ። መላ ቤተሰቡ ኢትዮጵያን ለዚህ ያበቁት የዎያኔ ዉሃ ተሸካሚዎች ናቸው። እኛ ድሮ የወሎ ልክስክስ ፖለቲካ ተምሳሌት እንላቸው ነበር። አሉ አይደል ለመጣው ግዢ ሚስት አቅረበው የሚልከሰከሱ! የኔ ወንድም እኔ የሱን ጉዳይ እንዲ ከቁም ነገር መቁተራቸው ገርምኝ ነው እንጂ የ360ም ዚፎዞ አይደለሁም። ልድገምልህ ዳኛቸው አንድም እከሌ የሚባል የፍልስፍና ተማሪ በሌለበት የዛሬ 7/8 አመት እንድሪያ ስራ ባይሰተው ዛሬ ይህን ባላልን ነበር። ያም ሆነ ይህ እይህ ሰው ለኔ ጉዳዬም ሃሳቤም አይደለም ።

Guest1
Member
Posts: 1926
Joined: 28 Dec 2006, 01:02

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by Guest1 » 20 Jul 2020, 02:00

horus
ከቤተሰቡ ጋር ማዛመድ ይቻላል ምክንያቱም ከቤተሰብ የምንወርሰው ሊኖር ስለሚችል። ስድቡ ግን ከልክ ያለፈ ነው! ከከፋ ጥላቻ ወጥተህ በተናገረውን ላይ ብታተኩር ጥሩ ነበር። የማይጠጣ፤ ሴት የማያሳድድ ፓለቲካ ኣለ እንዴ?

ወሎ ሆነ ሌሎች ክፍለ ሃገሮች የተለያየ ፓለቲካ የሚያራምዱ ሰዎች ነበሩ አሁንም መኖራቸው ሊያስገርም ኣይገባም። የሚመስለው ውሎን ልዩ የሚያደርገው ነገር ኣለ። ልደቱ ኣያሌው፤ የመጀመሪያው ጠ/ሚ የነበረው (ስሙ ጠፋኝ)፤ እንድርያስ እሸቴ፤ ገነት ዘውዴ...ዛሬ ከወሎ ኣንድ ታዋቂ ኣብዮተኛም ሆነ ተቃዋሚ ስም ጥራ። የለም። ዋናው ችግራቸው አማራም ኦሮሞም ነን የሚለው የፓለቲከኞቻቸው የቆየ ስብከትና በማንነታቸው ኣለመጽናት ይመስላል። የዛሬም ሆነ የድሮው ከሌላው የተለየ ኣቋም መሰረትም ይኸው ሳይሆን ኣይቅርም።

ስውዬው ፓለቲካ አያውቅም? ያውቃል። ተራ ወሬም ያውቃል። 300 ታንክ ይዘው አዲስ አበባ ይገባሉ። የሟቹ ሬሳ 35 ኪሎ ሚ ይዘው የተጓዙት በተቀናጀ ሴራ ነው፤ ባህል ማእከል ተደብቀው ወዘተ... ኣስቂኝም ነው። በአጠቃላይ የኣገራችን ችግር የተማረ ሰው/ምሁር በብዛት ኣለመኖሩ ሳይሆን ኣይቀርም።

Horus
Senior Member+
Posts: 30652
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by Horus » 20 Jul 2020, 02:27

Guest1

"ወሎ ሆነ ሌሎች ክፍለ ሃገሮች የተለያየ ፓለቲካ የሚያራምዱ ሰዎች ነበሩ አሁንም መኖራቸው ሊያስገርም ኣይገባም። የሚመስለው ውሎን ልዩ የሚያደርገው ነገር ኣለ። ልደቱ ኣያሌው፤ የመጀመሪያው ጠ/ሚ የነበረው (ስሙ ጠፋኝ)፤ እንድርያስ እሸቴ፤ ገነት ዘውዴ...ዛሬ ከወሎ ኣንድ ታዋቂ ኣብዮተኛም ሆነ ተቃዋሚ ስም ጥራ። የለም። ዋናው ችግራቸው አማራም ኦሮሞም ነን የሚለው የፓለቲከኞቻቸው የቆየ ስብከትና በማንነታቸው ኣለመጽናት ይመስላል። የዛሬም ሆነ የድሮው ከሌላው የተለየ ኣቋም መሰረትም ይኸው ሳይሆን ኣይቅርም።"

የልብ አክብሮቴን ልግለጽልህ ! ለምን በልኝ? በአለሌው ና በውል በማውቀው ዳኛቸው ላይ ስድብ ማብዛቴን ስለአረምከኝ ሳይሆን የወሎ ልክስክስ ፖለቲካ ስንል ትክክል ትርጉሙን ታሪካዊ እና ሶሺያል መሰርቱን በትክክል እንደ ምታቅ ስላየሁ ነው፣ በቃ ! የቀረው ሁሉ ንኡሳን ደቂቃን ነገሮች ናቸው ። ዳኛቸው ነገ ሟች ሰው ነው ፣ ለዘላለም የሚቀጥለው ያ ያልከው የወሎ ፖለቲካ ካልቸር ነው !!! ወያኔኮ በወሎ ሲያልፍ ተዘፍኖለት ነው ፤ ባምቦ ሲያልፍ ግን ተወግቶ ነው !!! ያ ነው የፖለቲካው ምድርና ሰማይ የሚለየው መስመር !!!

ሰላም

Guest1
Member
Posts: 1926
Joined: 28 Dec 2006, 01:02

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by Guest1 » 20 Jul 2020, 05:09

‘ያ ያልከው የወሎ ፖለቲካ ካልቸር ነው !!! ወያኔኮ በወሎ ሲያልፍ ተዘፍኖለት ነው ፤ ባምቦ ሲያልፍ ግን ተወግቶ ነው !!! ያ ነው የፖለቲካው ምድርና ሰማይ የሚለየው መስመር !!!’
የወሎ ፓለቲካ ‘እኛ ብዙ የመጠቁ ምሁራን ኣለን፤ ከሁሉም የበለጠ እኛ እናውቃለን’ ማለት ከሆነ፤ የድሮ የክፍለ ሃገር ፓለቲካ ጎጃሜ ጎንደሬ ወሎዪና ሸዋዬ የሚባለው ከሆነም በሁለቱም እስማማለሁ። ይህን ልክክስክስ ፓለቲካ ማለት ያዳግታል። ምሁራኑ የተከፋፈለው ክልሌነትና እኛ እናውቃለን ባይነትም ቢባል የተሻለ ነው። ኣንድ በጣም ታዋቂ የወሎ ፓለቲከኛ የወሎ ሪፐብሊክ እንመሰርታለን ብሎ ነበር እንደ ቀልድ።

በወሎ ወያኔን የተቀበሉት ምናልባት ጎንደርና ጎጃም ስለተቃወሙ (የባህር ዳር ተማሪዎች ተገለው ነበር) እና እንደኛ ተራማጅ ሃሳብ ያላቸው (ከእኛ ፓለቲካውን የበለጠ እናውቃለን ባይነት የመጣ) በማለት ሳይሆን ኣይቀርም። በኣምቦ የተዋጉት ከሆነ ምናልባት የመንግስቱ ሃ/ማርያም ደጋፊዎች (እነ መኢሶንና ማሌሪዶች መሸሸጊያ ስለነበር) በተጨማሪም የሰሜን ወረራ አድርገው ስላዩት ይሆናል። ወያኔ ድጋፍ ያገኘው ደርግ ስለተጠላ ብቻ ኣልነበረም። ሌላ ኣማራጭ ባለመኖሩም ጭምር ነው።

Abere
Senior Member
Posts: 10890
Joined: 18 Jul 2019, 20:52

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by Abere » 20 Jul 2020, 11:52

በ360 ላይ ዶር ዳ/ኛቸው ያደረገውን ውረፋ በተመለከት አንድ ሁለት ነገሮች።
በመጀመሪያ Horus የሰጠው አስተያዬት ዶ/ር ዳኛቸውን በግል በደንብ እንዴሚያውቀው በግልፅ ያሳያል። የእርሱን ባህርይ እና የግል የፓለቲካ ታሪክ አመላካች ይሆናል ባይ ነኝም። እኔ ስለ ዶ/ር ዳኛቸው ስም መስማት የጀመርሁት ወያኔ መጨረሻው የውድቀት ምዕራፍ ላይ በደረሰችበት ወቅት ነው። ያኔ ደግሞ ብዙ ምሁራን ይሁን የአገሬ ጉዳይ ያገባኛል የሚል ኢትዮጵያዊ ሁሉ ወያኔን እስከ ጠላ ድረስ ጆሮ ይሰጠው ነበር። ስለዚህ የጥራት ችግር ነበር ብል የተሳሳትሁ አይመስለኝም። ብዙ ምሁራኖች ብዙዎቻችን ግራ አጋብተውናል። እንዴት ቢሉ ከማንኛው የህብረተሰብ ክፍል ይበልጥ ቀድመው እጅ ነስተው ምንም ዓይነት ቅድመ ሁኔታ ሳያስቀምጡ ሰተት ብለው ወደ አገር ቤት ገብተው አገሪቷ አወዛጋቢ መንገድ ላይ እንድት ወድቅ አድርገዋል። በበኩሌ ለዚህ ውድቀት አገሪቷን የጣሏት እነርሱ ናቸው ባይ ነኝ። አንድ ጊዜ ወጥተው እንኳ በአፋቸው የደረሰውን የዘር ማፅዳት እና ሁከት ሲያወግዙ አልተሰሙም። ከሚገርሙኝ አንዱ Al- Mariam /ዓለማየሁ ኃይለማርያም/ ነው። በወያኔ ዘመን ምንጣፍ ምንጣፍ የሚያህል ትችት እና ዘለፋ ዘወትር ይፅፍ ነበር። አሁን እውነተኛው genocide ዕልቂት ሲፈፀም እርሱን የበላው ጅብ አልጮህ አለ። ለምን? እግረ መንገዴን ላንሳው ብዬ እንጅ በዙ ብዙ ቀለም የቆጠሩ በዕድሜ የበለፀጉ ድምፃቸው የለም። በድንገት ለናሙና ዶ/ር ዳኛቸው ብቅ ብሎ ምሁራዊ ዕይንታ የሌለው ጭፍን ዘለፋ በሌሎች አገር ወዳዶች ላይ መሰንዘር ትክክል አልነበረም። በመጀመሪያ ሁሉ መገናኛ ይዘጋልኝ የብልፅግና ብቻ ይጩህልኝ ስህተት ነው - የቀድሞው አደንቁረህ ግዛው ማለት ነው። በመቀጠል እንዴ እኔ የ 360 ሰዎች እጅግ ፅናት ያላቸው ናቸው ባይ ነኝ። ሳጥናዔል አጭበርብሮ ያልጣላቸው መላእክታት ዐይነት አብነት አያለሁ - በነገራችን ላይ እኔ የማንም ደጋፊ አይደለሁም ግን ትክክል የተናገረ የመሰለኝን አዳምጣለሁ። በእኔ አተያይ የሰጠው ከፓለቲካዊ አድርባይነት የመነጨ እንጅ ሚዛናዊ እና ምሁራዊ አምክንዮ የተደገፈ አይደለም። እንዴዚህ ዓይነት ትችት ደግሞ ገንቢ ሳይሆን አፍራሽ ነው ለአገሪቷ በአጠቃላይ። ህዝብ እኮ ማን የጥላቻ እና የሃሰት ፕሮፕጋንዳ እንዴሚቸረችር ያውቃል። በሁለተኛ ደረጃ የወሎ ክፍለ ሀገርን ከዳኛቸው ጋር በመደባለቅ የወሎን ገፀባህርይ ማሳል ስህተት ነው ባይነኝ። ዳኛቸው የአንድ የፊውዳል ቤተሰብ አባል ይመስለኛል። ስለዚህ የሚያንፀባርቀው የእርሱን ቤተሰባዊ ውርስ ጥቅም እና በስልጣን ልታይ እንጅ ማንንም አይወክልም። ዳኛቸው ወላዋይ ክልን 360 ላይ የሚወቀሰውን ሃብታሙ አያሌውን እንደዛ ማለት ይሆናል። በሁሉም ክፍለ ሀገር ዘንድ አድር ባይ በየጊዜው እንዴ እስስት ሀሳባቸውን እና መልካቸውን የሚቀያይሩ አሉ። ይኸ ተመሳስሎ የመኖር ግለሰባዊ ስልት ወይ እስትራቴጅ ነው። ፓለቲካ እና ፓለቲከኞች [ deleted ] የሚባሉት በእዚህ ይመስለኛል። እኔ እስከማውቀው በኢትዮጵያ ፓለቲካ ወሎ ብዙ ቁልፍ ሚና የተጫወተ ክፍለ ሀገር ነው። ሆኖም ግን የገዥ መደብ እና ህዝብ መለያየት አለብን ባይ ነኝ።

Wedi
Member+
Posts: 7959
Joined: 29 Jan 2020, 21:44

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by Wedi » 20 Jul 2020, 12:20

Abere እኔ እንደሚገባኝ ከሆነ Horus የወሎ ፖለቲካ እንል ነበር ነው ያለው፡፡ ይህ ደግሞ ከዛሬ 30+ ምናም አመት የተማሪዎች እንቅስቃሴ ውስጥ በነበሩነት ግዜ የነበረው ነው እየተናገረ ነው ያለው፡፡ ይህ ደግሞ በወቅቱ የሚባለ ከሆነ ምንም ማድረግ አይቻልም፡፡ ሲባል የነበርን ታሪክ በነበረብት ወቅትና ግዜ ሲባል እንደነበረው ነው መገለሽ ያለበት፡፡ አንት ወሎ የሚለው ወዲህ አመጣኸው፡፡ ነገሮችን በኮንቴክስት ማየት ያስፈልጋል ለማለት ነው፡፡

Abaymado
Member
Posts: 4191
Joined: 27 Sep 2017, 21:56

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by Abaymado » 20 Jul 2020, 12:29

What a fk? Horse has issues with this guy. This is not my first time reading such an awful comment by him, he was number of times in underrating and tarnishing his reputation. Once, while weyane was in power, this guy was highly praised by especially famous writers, intellectuals (particularly from opposition side)..... , so what happened now? horse looks envious on this guy for chasing ladies, may be because he has small and ugly dickkkk.

I rather prefer he come up with more modest way of comparison between Birhanu Nega and this guy. "He was supporter of weyane", so what? This is bulllshiiiit! grow up~! I am not defending this guy but it is too much.

Guest1
Member
Posts: 1926
Joined: 28 Dec 2006, 01:02

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by Guest1 » 20 Jul 2020, 13:23

@Abere
1. ኢትዮጵያ ወደ መቶ የሚጠጉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በነበሩበት ሁኔታ ውጭ በነበሩ ተቃዋሚዎች ላይ ክስ ማቅረብ ኣያሳምንም። በተለይ በትጥቅ ትግል የተሰማሩት ወደ አገር ቤት ለሰላማዊ ትግል መግባታቸው ትክክል ነበር። በነዛ በስም ኣይጠሬዎች ተጠርንፈው የነበሩት ግንቦት7 እና ኦነጎች ራሳቸው ነጻ ለማውጣትም ወደ ኣገርቤት የገቡ ሳይሆን ኣይቀርም። እዚያ ዳግም አይመለሱምና ጥሩ ነው።
2. ተቃዋሚ ምሁራኖች ለምን አይናገሩም ለምን ያንን ይህንን አላደረጉም ለተባለው እንደ እስክንድር ጀብደኛ አንሆንም ብለው እንጂ ዝም አላሉም። እየታዘቡ መሆናቸውን ገልጸዋል። ደግሞ የመናገር ነጻነት ኣለ ይባላል ግን እውን የመናገር መብት ኣለ? መጠራጠር ኣይከፋም። ኣሁን ጊዜው የመናገር መብት የሚፈተንበት ጊዜ ስለሆነ ለጊዜ ይተው።
3. ሌላ የተቃዋሚ ፓርቲዎች የማይናገሩት የሚከተላቸውን ፈርተው ብቻ ሳይሆን በደንብ ሳይደራጁና ራሳቸውን ሳያጠናክሩም ብዙ ለመናገርም ኣይደፍሩም። እርስ በርስ እነተነቆቆሩና ሃይላቸውን በተበታትነው ዛሬም እስከ 90? የሚሆኑ ፓርቲዎች በሆኑበት ኣገር ኣንድነት ለመፍጠርም ሲባል እንቅፋትም ላለመሆን ጥንቃቄ መውሰድ ስላለባቸው ይሆናል።
4. በገዢ መደብና በህዝብ መሃከል ልዩነት/ቅራኔ ኣለ። ምንጊዜም!! ሁለቱን ለማስታረቅ መሞከርማ ኣድርባይ ያሰኛል።
5. የወሎ ምሁራንን ሁሉንም ኣድርባይ ኣድርጎ ማስቀመጥ ትልቅ ስህተት ነው። ተራማጅም ኣለቅላቂም፤ ኣክራሪም፤ ጀብደኛም እንደ ማንኛውም ክ/ሃገር ኣለ። ጥያቄው የአማራም የኦሮሞም ደም ኣለብን የሚሉቱ ኢትዮጵያዊ ነን ማለቱን መምረጣቸው ትክክል ቢሆንም ቤተ አማራ ኖረው በአማራ ባህል ተክነው ኣማራ ኣይደለንም ማለት አይችሉም። አማራም ኢትዮጵያዊም መሆን ኣይቻልም የተባሉ የመስል ይዘበራርቃሉ። የዝህም መንስኤ ክልላዊነት ነው።
በነዝህ እስማማለሁ።
ስለዚህ የጥራት ችግር ነበር ብል የተሳሳትሁ አይመስለኝም። ብዙ ምሁራኖች ብዙዎቻችን ግራ አጋብተውናል። (ይህም የሆነው በቂ የተማረ ክፍል ኣለመኖር ሳይሆን ኣይቀርም።)

ይኸ ተመሳስሎ የመኖር ግለሰባዊ ስልት ወይ እስትራቴጅ ነው። ፓለቲካ እና ፓለቲከኞች [ deleted ] የሚባሉት በእዚህ ይመስለኛል። (ኣድርባይነት)

መልካም ቀን

Horus
Senior Member+
Posts: 30652
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by Horus » 20 Jul 2020, 14:46

ነገርን ነገር ያነሳዋል ይባላልና ጥሩ ውይይት እያደረጋችሁ ነው። እኔ በኢሳት መከፋፈል የማዝን፣ አሁን ደሞ ኢሳትም፣ 360ም፣ ዜና ቲዩብም ድንቅ ኢትዮጵያዊያን እንደ ሆኑ የማምን ሰው ነኝ ። ሁሉም ጀግኖቼ ናቸው፣ ዛሬም ማለት ነው ። በሃሳብ የመለያየት መብት አላቸው ። ኢትዮጵያን ከተለያየ ማዕዘን እያቀረቡ የትንተና ና ፖለቲካዊ ኢንተለጀንሳችን እያሰፉ ያለ አርበኞች ናቸው። የፖለቲካ ፍርፋሪ አሳዳጁ አድርባይ ዳኛቸው በምን ሞራል ብቃት ነው እነተቦርነን፣ እነኤርሚያስን እነሃብታሙን ኢትዮጵያን እንደ ካዱ አስመስሎ የሚዘልፋቸው? ያ ነው የነገሩ መነሾ!

ዎያኔ አማራ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላት ና ዋና ጠላት ነው ብሎ ኢትዮጵያን ለዚህ ሁሉ ጌኖሳይድ ሲያበቃኮ ዎይኔን ደግፎ የነሱን ቅሻሻ ዉሃ ያመላለሰ ልክስክስ ፈላስፋ የሚባለውን ቃል እንዲጠላ ያስደረገ ዳኛቸው ምትሉት የመሸታ ቤት ተራቢ ነው፣ በቃ ! ነገርን በስሙ ጠርታችሁ በሉት ። ያልተማረውን ያልተካነንበትን የፖለቲካ ፊሎሶፊ ሆነ የፖለቲካ ሳይንስ ውስጥ እየገባ ቁንጽል ቃላት የነ ኒኮሎ ማኪያቬሊን ስም በመጠቃቀስ አጉል የዙፋን አማካሪ ሊሆን ይዳዳዋል!! ይህም ሆነ ያ እኔ አብቅቻለሁ ፣ ድራማውን ሊቀጥል ይችላል!

Abere
Senior Member
Posts: 10890
Joined: 18 Jul 2019, 20:52

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by Abere » 20 Jul 2020, 15:12

[media wrote:Guest1 [/media]post_id=1087124 time=1595265794 user_id=60]
@Abere
1. ኢትዮጵያ ወደ መቶ የሚጠጉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በነበሩበት ሁኔታ ውጭ በነበሩ ተቃዋሚዎች ላይ ክስ ማቅረብ ኣያሳምንም። በተለይ በትጥቅ ትግል የተሰማሩት ወደ አገር ቤት ለሰላማዊ ትግል መግባታቸው ትክክል ነበር። በነዛ በስም ኣይጠሬዎች ተጠርንፈው የነበሩት ግንቦት7 እና ኦነጎች ራሳቸው ነጻ ለማውጣትም ወደ ኣገርቤት የገቡ ሳይሆን ኣይቀርም። እዚያ ዳግም አይመለሱምና ጥሩ ነው።
2. ተቃዋሚ ምሁራኖች ለምን አይናገሩም ለምን ያንን ይህንን አላደረጉም ለተባለው እንደ እስክንድር ጀብደኛ አንሆንም ብለው እንጂ ዝም አላሉም። እየታዘቡ መሆናቸውን ገልጸዋል። ደግሞ የመናገር ነጻነት ኣለ ይባላል ግን እውን የመናገር መብት ኣለ? መጠራጠር ኣይከፋም። ኣሁን ጊዜው የመናገር መብት የሚፈተንበት ጊዜ ስለሆነ ለጊዜ ይተው።
3. ሌላ የተቃዋሚ ፓርቲዎች የማይናገሩት የሚከተላቸውን ፈርተው ብቻ ሳይሆን በደንብ ሳይደራጁና ራሳቸውን ሳያጠናክሩም ብዙ ለመናገርም ኣይደፍሩም። እርስ በርስ እነተነቆቆሩና ሃይላቸውን በተበታትነው ዛሬም እስከ 90? የሚሆኑ ፓርቲዎች በሆኑበት ኣገር ኣንድነት ለመፍጠርም ሲባል እንቅፋትም ላለመሆን ጥንቃቄ መውሰድ ስላለባቸው ይሆናል።
4. በገዢ መደብና በህዝብ መሃከል ልዩነት/ቅራኔ ኣለ። ምንጊዜም!! ሁለቱን ለማስታረቅ መሞከርማ ኣድርባይ ያሰኛል።
5. የወሎ ምሁራንን ሁሉንም ኣድርባይ ኣድርጎ ማስቀመጥ ትልቅ ስህተት ነው። ተራማጅም ኣለቅላቂም፤ ኣክራሪም፤ ጀብደኛም እንደ ማንኛውም ክ/ሃገር ኣለ። ጥያቄው የአማራም የኦሮሞም ደም ኣለብን የሚሉቱ ኢትዮጵያዊ ነን ማለቱን መምረጣቸው ትክክል ቢሆንም ቤተ አማራ ኖረው በአማራ ባህል ተክነው ኣማራ ኣይደለንም ማለት አይችሉም። አማራም ኢትዮጵያዊም መሆን ኣይቻልም የተባሉ የመስል ይዘበራርቃሉ። የዝህም መንስኤ ክልላዊነት ነው።
በነዝህ እስማማለሁ።
ስለዚህ የጥራት ችግር ነበር ብል የተሳሳትሁ አይመስለኝም። ብዙ ምሁራኖች ብዙዎቻችን ግራ አጋብተውናል። (ይህም የሆነው በቂ የተማረ ክፍል ኣለመኖር ሳይሆን ኣይቀርም።)

ይኸ ተመሳስሎ የመኖር ግለሰባዊ ስልት ወይ እስትራቴጅ ነው። ፓለቲካ እና ፓለቲከኞች [ deleted ] የሚባሉት በእዚህ ይመስለኛል። (ኣድርባይነት)

መልካም ቀን
@Guest1

የሰጠሀቸውን አስተያየቶች አንዳንዶቹን እስማማለሁ በሌሎቹ ላይ ደግሞ የተለየ ግንዛቤ ነው ያለኝ። ለማንኛው ሀሳብህን አከብራለሁ። መቼም በዕይታ አንፃር 20/20 ይኖራል ከዘም የላቀ ወይም ዝቅ ያለ የዕይታ ዐድማስ (range) ይኖራል። ዋናው ቁም ነገሩ በሃሳብ ዙርያ መወያዬት ነው - የበለጠ ጥራት ለማገኜት።

1ኛ ) በመሠረቱ የኢትዮጵያ የተቃውሞ ፓለቲካ አስኳል ወይም ነርቭ ያለው ውጭ አገር ነው። አገር ቤት ያለው ህዝብ የመስዋዕት በግ ነው። ስለዚህ አገር ውስጥ 90 ይሁን ከዚያ በላይ ያሉ ተቃማዊ ፓርቲዎች ጉልበት ይሁን ተደማጭነት ዝቅተኛ ነው። አንዳንዶቹ ምስለ-ወያኔ ወይም ኦነግ ናቸው። ስለዚህ ትግሉን አስጨንግፈው ሌላ የፓለቲካ ግርዶሽ እና ጨለማ መንሥዔ የሆኑት በአንድ ዠምበር ጥሪ ሻንጣቸውን አንጠልጥለው አገር ቤት የገቡት ናቸው። ብዙ ተፅእኖ መፍጠር የሚችሉ እና የአገሪቷ ህግ እና ህገ-መንግስት፣ አገራዊ ዕርቅ ደረጃ በደረጃ ማረጋገጫ በማግኘት ኢትዮጵያን መታደግ ይችሉ ነበር።

2ኛ) ተደማጭነት እና ተፅእኖ ፈጣሪ ሊሆኑ የሚችሉት ምሁራን አዲስ አበባ ገብተው የሆቴል የጫጉላ ሽርሽራቸውን አቁመው የእስክንድርን ያህል ድምፃቸውን ቢያሰሙ ኑሮ ይህን ያህል ሰው አያልቅም፣ አገራዊ ቀውስ አይፈጠርም፣ ሀብት እና ኢኮኖሚ አይደቅም።በመሰረቱ እስክንድር ማድረግ የሚችለውን አከናውኗል። በደንብ ካጤን በዚህ 2 ዓመታት ውስጥ ድል ያደረገ እና ቁም ነገር ያከናወነው እስክንድ ብቻ ነው ብል ፍፁም ትክክል ነው። ወደ ኋላ ተመልሰን አዲስ አበባ የገጠማትን OPDO እና ኦነግ ሴራ እና ዕልቂት ቢደርስባት አሁን ምን አይነት ደረጃ ትደርስ ነበር። እኔ የሻሼመኔ ወይም የሀረር ከተሞችን ዕጣ ነው። የጥፋቱን ሚዛን ደግሞ እጅግ የላቀ ነው - የግዝፈት ልዩነቱ በፀሐይ እና በጨረቃ ነካከል ያህል ነው። ወርቅ ላበደረህ ጠጠር አይሁን። እንዴ በሬ አርሶ ያመረተውን እስክንድርን እንዴ ፍልፈል ከቆፈራት OPDO ፣ ኦነግ ወይም ሆዳም ምሁራኖች ጋር ማነፃፀር ኃጥያት ነው።

Wedi
Member+
Posts: 7959
Joined: 29 Jan 2020, 21:44

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by Wedi » 21 Jul 2020, 11:07

ይድረስ ለዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ!!

95% ኣርሶ ኣደር ለሆነው ለኢትዮዽያ ሕዝብ የማካቬሊ ፍልስፍና ምኑ ነው ?
========
ሰዉየው የፍልስፍና ምሁር ናቸው …..በመሆናቸውም ….ደጋግመው ….ደግመው ….ደጋግመው እንደልባቸው አየወጡ እየገቡ በሚመላለሱበት የሚዲያ ጣቢያ እየቀረቡ ትምህርት መስል ቅስቀሳ በማድረግም ይታወቃሉ ሰውየው።

ማካቬሊ እንዲህ ብሎ ነበር …ሶቅራጥስ የተባለው ፈላስፈ ደግሞ በአንድ ወቅት እንዲህ ብሏል… ሆሜር ያኔ እዚህ ላይ ይህንን የተናገረው ይህንን ለማለት ነው እያሉ ….. ሲይሻቸውም እንኯን በሬ ጠምዶ ለሚያርስ ገብሬ ቀርቶ ፊድል ቆጠርሁ ለሚለው ጎበዝም.. መዝገበ ቃላትን የሚያስፈልግ የእንግሊዘኛውን ጥቅስ በአንዴ ያንጎደጉዱትና ያችን ምሁራዊ አውቃለሁ ባይ አስተያየትና ፈገግታ ችረውን ለአንድ ደቂቃ ያህል ዝም ይሉና ትንፋሻቸውን ገዝተው ይቀጥላሉ ምሁሩ።

እንደ እኔ እንደ እኔ ሰውየው በዚች በደከምች አገር የሚኖረው ገበሬው ብቻ ሳይሆን… ለምጣኔ ሃብቱም ምሁሩም ሆነ ለኬምስትሪው …. ለፊዚክሱም ምሁሩም ሆነ ለባዮሎጅው …. ለአሪኪዎሎጅው ምሁሩም ሆነ ለኢንጅነሩ ….የማካቬሊ ፍልስፍና ወይም የሆሜር ወይም የሶቅራጥስ ፍልስፍና ለኢትዮዽያ ሕዝብ ምንም ፋያዳ እንደለለው የተረዱት አይመስለኝም ምክኒያቱ ደግሞ ግልጽ ነው … በሰላም ከቤቱ ወጥቶ በሰላም ለመመለሱ ዋስትና ለሌለው ሕዝብ ሶቅራጥስ ያኔ እንዲህ ብሎ ነበር ስትለው እየሰደብኸው ነው … እያሾህበትም ነው… እስቲ ግን እውነት ለመናገር አሁን የሚክቬሊ ፍልስፍና ለኢትዮዽያ ሕዝብ ምኑ ነው?

እንዲያው ነገር ነገር ያነሳዋል ነው …. ታሪክም እራሱን ይደግማል አንዳንዴ … እናም የአበዮቱ ዘመን ታሪክ ነው የተደገመብኝ ። ያኔ በአብዮቱ ዘመን የእን የመኢሶን … የእን ኢሕአፓ … የመንግሥትም ካድሬዎች በፈረቃ እየተመላለሱ ምንም የማናውቀውን እምቡጥ ወጣቶች ….ማርክስ እንዲህ ብሎ …ሌኒን እንደተናገረው …ማኦ በቀይ መጽሐፉ እንዲህ ብሎ እንደጻፍልን ….ስታሊን Nations and Nationalities በሚለው መጻፉ እንዳስተማረን ….እያሉ የሰባካ ቤቱን ይሞሉት ነበር። አዎ የእብደት ዘመን ነበር ዘመኑ። በሰው አገር በተደረጉት የለውጥ አብዮቶች ላይ ተመርኩዘው የተጻፉትንና የተነገሩት ሁሉ እኛዋ አገር ላይ መፈጸም አለበት ነበር የለውጡ ሂደት። ችግሩ ግን ማርክስ በነበረበት ዘመን አውሮፓ በኢንዱስትሪ አብዮት ተጥለቅልቃ እኛ ደግሞ ሁለት በሬ መግዛት የማይችል ገበሬ የሚኖርባት የሞለጨች ድኃ ሀገር ነው የነበረን ። እናም የማርክስ የገበያ ኢኮኖሚ ትንተና ለአገሬ ገበሬ በሬ መግዛት አልቻለም።

ታዲያ ምሁር በተለያየ ጊዜና ቦታ ወጣ ገባ እያሉ በየጊዜው የሚነግሩን የማካቬሊ ፍልስፍና ለአገሬ ሕዝብ የመኖር ሕልውና ሲሆን ማየት አልትይህ ብሎኛል …ምክኒያቱ ደግሞ ማካቬሊም ሆነ አምጦ የወለድው ፍልስፍናው ለኢትዮዽያ ምኑም ስላልሁነ ነው። አሁን አገራችን ላለችበት አጣብቂኝ መፍት ሄ ስለማይሆን ጭምርም ነው።

Befkadu Getachew

Guest1
Member
Posts: 1926
Joined: 28 Dec 2006, 01:02

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by Guest1 » 21 Jul 2020, 13:01

ማክያቬሊ የጻፈው ለመሪዎች ለአገር ገዢ ልኡል ነበር ስለ Leadership። ስለዝህ ሰውዬው መጥቀስ ነበረበት ለማሳሰብና ለማስተማርም። መልእክቱ ለጠ/ሚኒስተሩ ነው። መለስን የማክያቬሊ መጽሃፍ እንዲያነብ የመከሩትም ነበሩ። ኣዲስም ኣይደለም።

ማርክስ ስለየወዛደር አብዮት ነው። የሌኒንና የማኦ ኣፍሪክ፤ ኤዥያና ላቲን አሜሪካ የካፒታሊስት ስርኣት ያልገነቡ ኣገሮችን ይመለከታል። ሁለቱ የተያያዙ ስለሆኑ የግድ የሁሉም ስም መጠራቱ የማይቀር ነበር።

ኢትዮጵያ ወደ ካፒታሊስታዊ አብዮት (ሶሻሊስታዊ ኣብዮት የሚባለው በስህተት ነው) የተጀመረው ከመንግስቱ ንዋይ ጀምሮ ነው ማለት ይቻላል። የማኦንም ሆነ የሌኒን የአብዮትን የቀዳ ማን ነው? መንግስቱ። መንግስቱም ሶሻሊስት ይበል እንጂ (እነመኢሶን ኢሃኣፓም ጭምር) በመንግስቱ የተጀመረው መንግስታዊ ካፒታሊዝም ነበር። ከመንግስቱ ብኋላስ? ከጥቂት በስተቀር ሁሉም ማለት ይቻላል ወደ የግል ሃብት ተቀየሩ። የግል ካፒታሊዝም ለማራመድ ተሞከረ ግን እንደመንግስቱ ኢንዱስትሪ ለመገንባት ኣልተሞከረምና ወደ ኋላ እንደመመለስም ነበር። ለምሳሌ በሃይለስላሴ ዘመን እንደነበር የግል ባለሃብቶች መፍጠር። ስለዝህ ኢትዮጵያ ኣሁንም ካፒታሊስታዊ ስርኣት ለመገንባት በምታደርገው ጥረት ከሌሎች አገሮች ልምድ መቅሰም አይከለክልም (ማኦና ሌኒን) የግድም ነው ከስህተታቸውና ከውጤታማነታቸው ለመማር።

በዝህ እስማማለሁ
በሰው አገር በተደረጉት የለውጥ አብዮቶች ላይ ተመርኩዘው የተጻፉትንና የተነገሩት ሁሉ እኛዋ አገር ላይ መፈጸም አለበት ነበር የለውጡ ሂደት። ትክክል። በአገራችን ነባራዊ ሁኔታን ያገናዘበ ኣልነበረም። 1. ለምሳሌ በመንግስቱ የተጀመረው ካፒታሊስታዊ ስርኣትን እንደ ሶሻሊስታዊ ስርኣት በመውሰድ በስመ ሶሻሊዝም የተደረጉ ስህተቶች እስካሁንም ኣለማረም ምንም እንኳን ሁሉም ነገር ወደ ግል ሃብት ቢዘዋወርም። ለምሳሌ መሬት ላራሹና የትርፍ ቤቶች ኣዋጅ። ወደ ኢንዱስትሪ አብዮት የሚወስደውን ጎዳና መንግስታዊ ካፒታሊዝምን በውጭ ኢንቬስትመንት መተካት ወዘተ... ኢኮኖሚን በማሳደግ፤ የህዝብ ኑሮን ከፍ ማድረግ፤ ስራ ኣጥነትን ማጥፋት ወይም መቀነስ፤ የመናገርና የመጻፍ መብት ወዘተ... ለማፋጠንም ከጥገኝነትም መላቀቅ አልቻለም።

ከድሮው መማር የግድ ነው።የሚሻለው ደግሞ በኣሁኑ ላይ ማተኮር። ምን እየሰማን ነበር? ከደርግ ብኋላ ልማታዊ መንግስት፤ ሊብራሊዝም፤ እውነተኛ ፌድራሊዝም፤ መደመር ምን? ኣገራዊ ናቸው?

Horus
Senior Member+
Posts: 30652
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by Horus » 21 Jul 2020, 14:47

Guest1

ውይይቱ እንደዚህ ቁም ነገር አዘልነት መዞሩ ጥሩ ነው ። የኒኮሎ ማኪያቬሊ የፖለቲካ ታክቲክ ምከር ለዳኛቸው አዲስ ሆነ እንጂ ከ700 አመት በላይ እድሜ አለው ። መንግስቱ ሃይለ ማሪያም ሃይለ ስላሴን አስሮ ቤት መጻህፍፍታቸው ሲበርብር ያገኘው የአማርኛ ትርጉም የማኪያቬሊ "መስፍኑ" የሚባለውን መጽሃፉ ነበር ። የመሳፍንቶችና የገዢዎች አስተዳደር፣ አገዛዝ፣ የፖለቲካ ታክቲክ ሸርና ጥበብ ማስተማሪያ ነው። ዛሬ በዘመናዊ ይዘቱ 'የፖለቲከ መሪነት' (ፖለቲካል ሊደርሺፕ) በሚለው ክህሎት ስር ሲመደብ ዋና ቁልፍ ጭብጡ 'ያገዛዝ ጥበብ ' (እስቴትክራፍት) ይባላል። እኔ ስል የነበረው ይህ ሁሉ የዳኛቸው ትምህርት ወይም ኤክስፐርቲስ አይደለም ። እሱ ልክ ልጆች እንደ ነበርንበት ዘመን ለጉራ በቁንጽል የጠቀሰውን ልንገር ።
መስፍን ሜዲቺ ማኪያቬሊን እንዲህ ብሎ ይጠይቀዋል፤ ለግዛቴ መጽናት የሚሻለው ሰዎች ቢወዱኝ ነው ወይስ ቢፈሩኝ? ይለዋል ። ማኪያቬሊ መልሶ፣ ቢቻል ቢቻል ሰዎች ወደውህ መግዛት፤ ያ ካልቻልክ ግ ን ሰዎች ፈርተው ቢገዙልህ ነው ይለዋል ። በመሰረቱ የሚኪያቬል ምክር በዚህ ዙሪያ የተዋቀረ ታክቲኮች ዝርዝር ነው ። ማለትም ሰዎችን በጉቦ በማማለል፣ ባድር ባይነታቸው መያዝ ፣ ያ ካልሰራ በሀይል፣ በሸር፣ በመከፋፈል መግዛት ወዘተ ። እና ባለፈው የዳኛቸው ኢንተርቬው ሊል የሞከረው አቢይ በመወደድ ሊገዛቸው ስላልቻለ እነኦነግን ማለቱ ነው፣ አሁን ሃይል የመጠቀሚያ ወቅቱ ነው ማለቱ ነው ። ግን አንድም ሰው ይህን ማለቱን አያቅም ። በፍካዱ ያለው እዚህ ላይ ነው አግባቡ።

ስንቱ አርሶ አደር ነው ይህን የማኪያቬሊ ታክቲክ አቢይ እንዲሰራበት ዳኛቸው መምከሩ የገባቸው? እኔ ደሞ የምለው ዳኛቸው የፖለቲካ ፊሎሶፊና የፖለቲካ ሳይንስ ተማሪ ስላልሆነ ያለው እንኳ ባግባቡ ሊል ብቃት የለውም። ለምሳሌ በኢትዮጵያ የጎሳ መንግስት ወይም ኤቲኒክ እስቴት አገዛዝ የማኪያቬሊ ታክቲኮች አይሰሩም ። የሚኪያቬሊ ሞዴል የሚሰራው ህብረተ ሰቡ በጎሳ በተከአፈለበት እና መንግሥቱ ባንድ ጎሳ በተያዘበት ሳይሆን ህዝቡ አንድ ሆኖ ገዢዎች በመንግስት ውስጥ ለሃይል በሚሿከቱበት ሁኔታ ነው።

ነገርን ነገር ያነሳዋልና አዲሱ ትውልድ በዚህ ሳቢያ ስለ የመንግስት ጥበብ (እስቴትክራፍት) እውቀት ማዳበሩ በጣም ተፈላጊ ነው። ያ ነው የፖለቲካ መሪነት የሚባለው ። የፖለቲካ ሳይንስ ወይም የፖለቲካ እውቀት ተግባራዊ ሲሆን እስቴትክራፍት እንጂ ሌላ አይደለም ። ይህ ደሞ የዳኛቸው ኤክስፐርቲስ አይደለም ።

sun
Member+
Posts: 9312
Joined: 15 Sep 2013, 16:00

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by sun » 21 Jul 2020, 15:57

Horus wrote:
21 Jul 2020, 14:47
Guest1

ውይይቱ እንደዚህ ቁም ነገር አዘልነት መዞሩ ጥሩ ነው ። የኒኮሎ ማኪያቬሊ የፖለቲካ ታክቲክ ምከር ለዳኛቸው አዲስ ሆነ እንጂ ከ700 አመት በላይ እድሜ አለው ። መንግስቱ ሃይለ ማሪያም ሃኢለ ስላሴን አስሮ ቤት መጻህፍፍታቸው ሲበርብር ያገኘው የአማርኛ ትርጉም የማኪያቬሊ "መስፍኑ" የሚባለውን መጽሃፉ ነበር ። የመሳፍንቶችና የገዢዎች አስተዳደር፣ አገዛዝ፣ የፖለቲካ ታክቲክ ሸርና ጥበብ ማስተማሪያ ነው። ዛሬ በዘመናዊ ይዘቱ 'የፖለቲከ መሪነት' (ፖለቲካል ሊደርሺፕ) በሚለው ክህሎት ስር ሲመደብ ዋና ቁልፍ ጭብጡ 'ያገዛዝ ጥበብ ' (እስቴትክራፍት) ይባላል። እኔ ስል የነበረው ይህ ሁሉ የዳኛቸው ትምህርት ወይም ኤክስፐርቲስ አይደለም ። እሱ ልክ ልጆች እንደ ነበርንበት ዘመን ለጉራ በቁንጽል የጠቀሰውን ልንገር ።
መስፍን ሜዲቺ ማኪያቬሊን እንዲህ ብሎ ይጠይቀዋል፤ ለግዛቴ መጽናት የሚሻለው ሰዎች ቢወዱኝ ነው ወይስ ቢፈሩኝ? ይለዋል ። ማኪያቬሊ መልሶ፣ ቢቻል ቢቻል ሰዎች ወደውህ መግዛት፤ ያ ካልቻልክ ግ ን ሰዎች ፈርተው ቢገዙልህ ነው ይለዋል ። በመሰረቱ የሚኪያቬል ምክር በዚህ ዙሪያ የተዋቀረ ታክቲኮች ዝርዝር ነው ። ማለትም ሰዎችን በጉቦ በማማለል፣ ባድር ባይነታቸው መያዝ ፣ ያ ካልሰራ በሀይል፣ በሸር፣ በመከፋፈል መግዛት ወዘተ ። እና ባለፈው የዳኛቸው ኢንተርቬው ሊል የሞከረው አቢይ በመወደድ ሊገዛቸው ስላልቻለ እነኦነግን ማለቱ ነው፣ አሁን አይል የመጠቀሚያ ወቅቱ ነው ማለቱ ነው ። ግን አንድም ሰው ይህን ማለቱን አያቅም ። በፍካዱ ያለው እዚህ ላይ ነው አግባቡ።

ስንቱ አርሶ አደር ነው ይህን የማኪያቬሊ ታክቲክ አቢይ እንዲሰራበት ዳኛቸው መምከሩ የገባቸው? እኔ ደሞ የምለው ዳኛቸው የፖለቲካ ፊሎሶፊና የፖለቲካ ሳይንስ ተማሪ ስላልሆነ ያለው እንኳ ባግባቡ ሊል ብቃት የለውም። ለምሳሌ በኢትዮጵያ መንግስት ወይም ኤቲኒክ እስቴት አገዛዝ የማኪያቬሊ ታክቲኮች አይሰሩም ። የሚኪያቬሊ ሞዴል የሚሰራው ህብረተ ሰቡ በጎሳ በተከአፈለበት እና መንግሥቱ ባንድ ጎሳ በተያዘበት ሳይሆን ህዝቡ አንድ ሆኖ ገዢዎች በመንግስት ውስጥ ለሃይል በሚኳከቱበት ሁኔታ ነው።

ነገርን ነገር ያነሳዋልና አዲሱ ትውልድ በዚህ ሳቢያ ስለ የመንግስት ጥበብ (እስቴትክራፍት) እውቀት ማዳበሩ በጣም ተፈላጊ ነው። ያ ነው የፖለቲካ መሪነት የሚባለው ። የፖለቲካ ሳይንስ ወይም የፖለቲካ እውቀት ተግባራዊ ሲሆን እስቴትክራፍት እንጂ ሌላ አይደለም ። ይህ ደሞ የዳኛቸው ኤክስፐርቲስ አይደለም ።
So what if the 700 years divide and rule Machiavelli's arts and crafts may not appeal to some guys and gals especially during the current 21st century on going new changes and transformations. One of the biggest political problems in Ethiopia is elites' blind and wholesome willing uncritical importation of alien ideologies, methods and tactics straight from the books rather than digging deep and mining precious indigenous philosophies and ideologies, updating and applying them to effectively solve our current problems.

Look at how Mengistu's Stalinist ideology, Meles's Maoist Pol Potist, Enver Hoxhaist communist ideologies have ruined the country regardless of some of its token contributions
. 8)
Last edited by sun on 21 Jul 2020, 17:17, edited 2 times in total.

tlel
Member
Posts: 1559
Joined: 28 Dec 2019, 14:24

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by tlel » 21 Jul 2020, 17:02

የኢሃፓም ሆነ በስውር ከ ሻብያና ከህዋሃት የሚሰሩ እንደዚህ ኣይነት ግለሰቦች በደንብ መመርመር ህዝብ ኣለበት። የኣዲስ ኣበባ ይኒቨርስቲ የተማሪውን ኣንጎል የገደሉት በተቀነባበር ዘዴ እነዚህ ግለሰቦች ናቸው እንድሪያስና ዳኛችው። የህይወት ታሪካቸው ጠለቅ ተደርጎ መታውቅ ኣለበት። ከሻብያ ህዋሃት ግንኙነታቸው በኢሃፓ፣ በወሎ ውስጥ ሃይለስላሴን በመጥላት የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ቂም በቀል እስካሁን እያካሄዱ ናቸው። ተዉ የሚላቸው የለም መልካቸውን እየቀየሩ ብቅ ይላሉ። እንድርያስ ግማሽ ኤርትራዊ ነው። ኢሃፓም ነው። ለዚህ ነው ኢሃፓዎች ላይ ማተኮር ካሁን ወዲህ፣ ተስፋ የነበረው በ ብርሃኑ ንጋና ኣንዳርጋቸው ፅጌ ነበር። ግን ኣሁን ኢሃፓ እስካሁን ኢትዮዽያውያንን እየበላ ነው ማለት ማፈር ኣይደለም። ኣሁንም በተግባር ደካማነታቸውንና የዘረኞች የነፃውጪዎች መዳብ እየሆኑ እየቀጠሉ ነው። ኢትዮዽያውያንን እያስበሉ ነው ያሉት። እንደውም ሶማልያ ኢትዮዽያን ሲወጋ በዚያድ ባሬ ጊዜ፣ ከሃዋሃትና ከሻብያ ጋር ሆነው ኢሃፓዎች ኢትዮዽያን የወጉ ናቸው። ኣላመቸው ምን እንደሆነ እስከ ዛሬ ድረስ ግልፅም ኣይደለም። የነፃውጪዎች እንኳን ግልፅ ነው፣ ኢሃፓ የነሱ መሳርያ እንጂ ምንም ኣይጠቅሙም። የመሰለኝ የነበረው ኣላማቸውን ትተው ወደ ኢትዮዽያ ትግል ነበር ግን፣ ባዶ ናቸው።

tlel
Member
Posts: 1559
Joined: 28 Dec 2019, 14:24

Re: የኢትዮ360 እና ዳኛቸው አሰፋ አወቅኩሽ ናቅኩሽ

Post by tlel » 21 Jul 2020, 17:16

ጋጊም ሆንክ ገስት፩፣
ከዚህ ከንቱ ጥፋት ሌላ ማን ኣለ የኢትዮዽያን ወጣት እውቀታቸውን ያወደሙ እውነት ሊኢትዮዽያ ባሁን ሰካራምነታቸው ኣገርን ይመራሉ ብላችሁ ታስባላችሁ

የወሎ ውስጥ ይተደረገው የኢሃፓ፣ወሎ ገራገሩን ቦታ ተጠቅመው የኤርትራ ሴረኞች ወጣቱን ሃይለስላሴን እንዲጠሉኣቸው በድርቅ ጊዜ የተደረገበት ቦታ ነው። ኣሁንም ብዙ ሴረኞች ኣሉ፣ ግን ሚስጥር ነው ኣይነገርም ኢሃፕ ለምን እንዴት እንደተመሰረተ። ኢሳያስና ኣጎቱ ወሎ ውስጥ ማንና ለምን ኖሩ፣ ድርቅ ወሎ ውስጥ ላምንና በማን ተፈጠረ እስኪ ሂዱና የባንክ ሌባው ታምራ ላይኔን መጠየቅ ጥሩ ነው። እንዴት የኢትዮዽያ ህዝብ ስቃይ እንዴት እንደተጀመረ። መፅሃፍ ቢፃፍ ከፍቅር እስከ መቃብር ብዛት የወጣዋል። ኣሁን ያንን ጉድ ለመደበቅ እንጂ ለኢትዮዽያ ማንም ኣዝኖ ኣይደለም። ኢትዮዽያ በራሱ ታግሎ እነዚህ ነፃውጪዎችን እስከ ኢሃድግ ውስጥ የተበከሉትን ጨምሮ ማስወገድ ነው። ዶር ኣብይ ወይም ለማ ማንም የሚቃውማቸው ኣይኖርም ነበር ኣገሪቱን ቢያስተካክሉ ኖሮ።

Post Reply