Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
MatiT
Senior Member
Posts: 11549
Joined: 16 Feb 2013, 10:18

°° የትግራይ_ተወላጅ_የሆኑ_የአዲስ_አበባ_ብልፅግና_ፓርቲ #አመራሮች_የአቋም_መግለጫ!

Post by MatiT » 21 May 2020, 17:14

#የትግራይ_ተወላጅ_የሆኑ_የአዲስ_አበባ_ብልፅግና_ፓርቲ #አመራሮች_የአቋም_መግለጫ!

እኛ የትግራይ ተወላጅ የሆንን የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ አመራሮች፣ ባለፉት ቀናት ስለአጠቃላይ የአዲስ አበባ የፓርቲያችን መዋቅር እንዲሁም ኮቪድ 19፣ የምርጫ መራዘምና የህግ አማራጮች በሚል ርእስ ስናደርግ የነበረውን ውይይት በማጠናቀቅ የሚከተለውን የጋራ አቋም መግለጫ አውጥተናል፡፡

የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦
ፓርቲያችን ብልፅግና የመላው ኢትዮጵያውያን ፓርቲ ሆኖ፣ ሁሉንም ህዝቦች በፍትሃዊነትና በእኩልነት የሚያሳትፍ አደረጃጀት ፈጥሮ በመንቀሳቀስ ላይ እንደሆነ ይታወቃል፡፡
እኛ በተለያየ የአመራር ቦታ ያለን የቀድሞ የሕወሓት አባላት፣ በብልፅግና ፓርቲ ታቅፈን ለመንቀሳቀስ እና የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ እውን ለማድረግ ካለን ፅኑ ፍላጎት በገዛ ፍቃዳችን ስንቀላቀል፣ ፓርቲያችን መላውን ህዝባችንን በተለይም ባለፉት አመታት ምንም ሳይጠቀም እንደተጠቀመ ተቆጥሮ በስሙ ሲነገድበት የነበረውን የትግራይ ህዝብን ተጠቃሚ ማድረግ የሚችልና የህዝቡንም ቀጣይ እጣ ፋንታ ብሩህ ማድረግ እንደሚችል ካለን ጠንካራ ልባዊ እምነት የተነሳ ነው፡፡

የትግራይ ህዝብ ለመብቱ እና ለነፃነቱ ውድ ዋጋ የከፈለ፣ ከኢትዮጵያዊ ወንድም እና እህቶቹ ጋር በጋራ መኖር የሚፈልግ ታላቅ ህዝብ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ ትግሉ በጥቂት የራሳቸውን የግል ስልጣን ለማደላደል በሚፈልጉ ቡድኖች ታጥሮ፣ የታገለለትን መብት በሚገባ ሳይጎናፀፍ ዛሬም ታፍኖ እኔ አውቅልሃለው በሚል መርህ ከሌሎች ወንድሞቹ እና እህቶቹ ጋር የመገለል ስሜት እንዲያድርበትና በጥርጣሬ እንዲኖር እየተደረገ ይገኛል፡፡

የትግራይ ህዝብ ከታገለላቸው አላማዎች አንዱና ዋነኛው ህብረ-ብሄራዊ ፌደራሊዝም ስርዓት በሃገራችን እውን እንዲሆን ነው፡፡ ነገር ግን እነዚህ ጥቂት እኩይ አላማ ያላቸው ቡድኖች “ብልፅግና አሃዳዊ ስርዓት ነው”! የሚል የተዛባ ፕሮፖጋንዳ እየነዙ ቀላል የማይባል ቁጥር ያላቸው ወገኖቻችንን እያሳሳተ ይገኛል፡፡ ሆኖም ብልፅግና ለእውነተኛ ህብረ-ብሄራዊ አንድነት በመከባበር እና በመተማመን ላይ የተመሰረተ የህዝቦች ግንንነት ለማጠንከር የሚሰራ ፓርቲ እንጂ በፌደራሊዝም ስም የጥቂቶችን ፍላጎት ለማራመድ የማይሰራ ፓርቲ ነው፡፡

ህወሓት አሁንም የትግራይ ህዝብ የለውጥ ተጠቃሚ እንዲሆን ከማድረግ ይልቅ የቀድሞ የማታለል ሴራውን እየተገበረበት ይገኛል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ህብረተሰብ እና መንግስት በሃገራችን የተከሰተውና ቁጥሩ እየጨመረ ያለውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሺኝ ለመከላከል ከፍተኛ ርብርብ በሚደረግበት “ምርጫ ካልተደረገ የሚል ግትር አቋሙም ለህዝቡ ደህንነት ደንታ እንደሌለው በግልፅ አሳይቷል፡፡

ምርጫ የህዝብ ዲሞክራሲያዊ መብት መሆኑን እናምናለን፡፡ ነገር ግን የህዝብን ደህንነት ቅድሚያ መስጠት ስለሚገባ፣ በፓርቲያችንና በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ መራዘም የተያዘውን አቋም ተገቢና ትክክለኛ እርምጃ መሆኑን እናምናለን፡፡ ቀጣይ እርምጃዎችም ህገመንግስቱንና ህገመንግስታዊ ስርዓቱን ባከበረ መልኩ መካሄድ እንደሚኖርበትም የማያወላላል አቋም አለን፡፡

በነበረን የውይይትና የምክክር መድረክም የሚከተለውን ባለ አምስት ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥተናል፡፡

1ኛ መንግስት የምርጨውን መራዘም አስመልክቶ እየሄደበት ያለው ህጋዊና ህገመንግስታዊ የመፍትሄ አቅጣጫ ፤የህዝቡን ደህንነት ቅድሚያ የሚሰጥ፤ አሁን የተጋረጡብንን አደጋዎች እንደ ሃገር ትኩረታችን ሳይዘነጋ እንድንከላከል የሚያግዝ በመሆኑ፣ የምንደግፈውና ለተግባራዊነቱም ከፓርቲያችን እና ህዝባችን ጎን በመሆን የምንታገል መሆኑን እንገልፃለን፡፡

2ኛ በክልል ደረጃ ምርጫ ማካሄድ የማይቻልና ኢ-ህገመንግስታዊ ነው፡፡ ስለሆነም ህወሓት በክልል ደረጃ ምርጫ አካሂዳለው ብሎ መነሳቱ ፍፁም ህገወጥና የሃገሪቱን ህጎች መናድ በመሆኑ በአስቸኳይ ከድርጊቱ እንዲቆጠብ እናሳስባለን፡፡

3ኛ ብልፅግና የአዲሱ ትውልድ ፓርቲ ነው፡፡ ይህ ፓርቲ የትግራይን ህዝብ ከሌሎች ወንድምና እህት ህዝቦች በጋራ የልማት እና የእውነተኛ ዲሞክራሲ ተጠቃሚ ለማድረግ በከፍተኛ ሁኔታ እየሰራ ይገኛል፡፡ ነገር ግን በተለመደ የማጠልሸት ተግባራቸው ብልፅግና የትግራይን ህዝብ እንደሚጠላ በማስመሰል የራስን ስልጣን ለማቆየት የሚያደርጉትን ጥረት በመቃወም የብልፅግና ጉዞው ተጠቃሚ እንዲሆን ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

4ኛ የትግራይ ህዝብ ከሌሎች ወንድም እህቶቹ ጋር በጋራ መኖር የሚያውቅ፣ ለኢትዮጵያዊ አነድነት ብዙ ዋጋ የከፈለ ነው፡፡ በመሆኑም ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በሰላምና በመከባበር በወንድማዊ ስሜት ሆነን፣ አብሮነታችንንና አገራዊ የለውጥ እንቅስቃሴያችንን እንድናፋጥን እየጠየቅን፣ ይህን ከፋፋይ ተግባር በጋራ ሆነን እንድንታገለው ጥሪ እናቀርባለን፡፡

5ኛ በመጨረሻም፣ የህዳሴ ግድባችን ለሃገራችን የብልፅግና ጉዞ ወሳኝና እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ እኛ የትግራይ የብልፅግና ፓርቲ አመራሮች በግድቡ ላይ የሚደረግ ማንኛውም ውጫዊ ጫናና ጣልቃ ገብነት በፍፁም የማንቀበለውና ፤ለግድቡ እውን መሆን አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆናችንን እንገልፃለን፡፡

ግንቦት 2012
አዲስ አበባ

Sam Ebalalehu
Member
Posts: 3639
Joined: 23 Jun 2018, 21:29

Re: °° የትግራይ_ተወላጅ_የሆኑ_የአዲስ_አበባ_ብልፅግና_ፓርቲ #አመራሮች_የአቋም_መግለጫ!

Post by Sam Ebalalehu » 21 May 2020, 18:21

I agree wholly with the five points they mentioned. It is especially essential to laser focus on the fifth one. Ethiopia should and will not allow any foreign power to dictate its wish regarding the dam on her. If individuals , or groups, or a party works with foreign power to sabotage the dam that spells treason.
There are some who argued Egypt will bomb the dam to the ground. That might be possible.
But I believe the Egyptian politicians have the brain to entertain these two thoughts. One after bombing the dam, Ethiopia might not allow the Nile to flow to Egypt as it had been, she might increase irrigation system using the river for example. Second as our dam might be a target of the Egyptian airfoce, the Aswan dam will be the target of Ethiopian Air Force too. Egypt has no choice but to accept the vey generous proposal Ethiopia offered.

Post Reply