Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum


Revelations
Senior Member+
Posts: 33713
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: Ethiopia Vote Agency Queries Key Opposition Leader’s Citizenship [Bloomberg]

Post by Revelations » 12 Feb 2020, 08:11

Please wait, video is loading...

Revelations
Senior Member+
Posts: 33713
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: Ethiopia Vote Agency Queries Key Opposition Leader’s Citizenship [Bloomberg]

Post by Revelations » 12 Feb 2020, 08:20

ምርጫ ቦርድ የጃዋር ኢትዮጵያዊነትን አስመልክቶ ማብራሪያ እንዲሰጠው ኢሚግሬሽንን ጠየቀ



በቅርቡ ኦፌኮን የተቀላቀሉት የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ መስራች አቶ ጃዋር መሃመድን ፓርቲያቸው ኢትዮጵያዊ ናቸው የሚል የአባልነት ማረጋገጫ መስጠቱን ተከትሎ የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ዜግነታቸውን መልሰው የሚያገኙበትን ሂደት ማብራሪያ እንዲሰጠው ምርጫ ቦርድ ኢሚግሬሽንን ጠይቋል።

የምርጫ ቦርድ የካቲት 2፣ 2012 በፃፈው ደብዳቤ አቶ ጃዋር የኢትዮጵያ ዜግነታቸውን መልሰው በማግኘት ሂደት ላይ እያሉ ፖርቲያቸው ኢትዮጵያዊ ናቸው የሚል የአባልነት ማረጋገጫ መስጠቱን ጠቅሷል።

በአገሪቱ ህግ መሰረት ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌላቸው ግለሰቦች በፖለቲካ መሳተፍ ስለማይችሉ ከዚህ ቀደም ምርጫ ቦርድ አቶ ጃዋር ኢትዮጵያዊ ዜግነታቸውን መልሰው አግኝተው ከሆነ ይሕንን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ወይም ሰነድ ከደህንነት፣ ኢሚግሬሽን እና ስደተኞች ጉዳይ ባለስልጣን እንዲያቀርቡ ለፓርቲው ሁለት ጊዜ በደብዳቤ ጠይቋል።

ኦፌኮ በምላሹም ለምርጫ ቦርድ በላከው ደብዳቤ አቶ ጃዋር መኖሪያቸውን ኢትዮጵያ ማድረጋቸውን ጠቅሶ፣ የሌላ አገር ዜግነታቸውንም በመተው፣ ኢትዮጵያዊ ዜግነታቸው እንዲመለስላቸው ለሚመለከተው የመንግሥት አካል በማመልከታቸው ኢትዮጵያዊ ናቸው የሚል ደብዳቤ ፅፏል።

በተጨማሪም ምርጫ ቦርድ ከኦፌኮ ደረሰኝ ያለው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው በትውልድ ኢትዮጵያዊ ለሆነ ሰው ኢትዮጵያዊ ዜግነትን መልሶ ማግኘትን በተመለከተ ከየትኛውም የመንግሥት አካል ሰነድ ወይም ማስረጃ ሰርቲፊኬትን ማግኘት የሚደነግግ ህግ የለም ብሏል።

በዚህም መሰረት አቶ ጃዋር የኢትዮጵያዊነታቸውን ማስረጃ ሰነድ ፓርቲው እንዲያቀርብ መጠየቁ አግባብነት የለውም የሚል መከራከሪያ ሃሳብ ከማቅረብ በተጨማሪ አቶ ጃዋር ኢትዮጵያዊ ናቸው የሚል ምላሽ ለምርጫ ቦርድ ሰጥቷል።

ምርጫ ቦርድ በበኩሉ ፓርቲው ሰነድ ማቅረብ አይገባንም የሚለውን ከሃገሪቱ አዋጅ አንፃር በመፈተሽ ውሳኔ ማሳለፍ ቢችልም፤ ምናልባት ይህ ሁኔታ የዜግነትን ጉዳይ ለመመርመርና ለመወሰን ስልጣን ካለው የኢሚግሬሽን ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ አሰራር ሂደት ጋር ሊጣረስ ይችላል፤ እንዲሁም ወደፊትም የሚመጡ ጥያቄዎችን ማስተናገድ ይቻል ዘንድ ውሳኔ እንዲያስተላልፍ መጠየቁን ደብዳቤው አትቷል።

ይህንን መሰረት በማድረግ በትውልድ ኢትዮጵያዊ የሆነ፣ የሌላ አገር ዜግነት ያለው ሰው መኖሪያውን በኢትዮጵያ ካደረገ፣ የሌላ አገር ዜግነቱን ከተወ እንዲሁም ኢትዮጵያዊ ዜግነቱ እንዲመለስለት ለባለስልጣኑ ካመለከተ ዜግነትን ያለ ኤጀንሲው ውሳኔ ወዲያው ያገኛል ወይስ አያገኝም የሚለው ላይ ምላሽ እንዲሰጠው ምርጫ ቦርድ በደብዳቤው ጠይቋል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ማብራሪያውን እስከ የካቲት 9፣2012 ዓ.ም ድረስ እንዲልክም መጠየቁን የምርጫ ቦርድ ደብዳቤ ያስረዳል።

ለረጅም ዓመታት የአሜሪካ ዜጋ እንደሆኑ የሚታወቁት አቶ ጃዋር መሐመድ በኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ አባል ሆነው በቅርቡ ቀጥተኛ የፖለቲካ እንቀስቃሴ ውስጥ መግባታቸው ይታወሳል።

Revelations
Senior Member+
Posts: 33713
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: Ethiopia Vote Agency Queries Key Opposition Leader’s Citizenship [Bloomberg]

Post by Revelations » 12 Feb 2020, 08:37

Please wait, video is loading...


Revelations
Senior Member+
Posts: 33713
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: Ethiopia Vote Agency Queries Key Opposition Leader’s Citizenship [Bloomberg]

Post by Revelations » 12 Feb 2020, 15:49

Please wait, video is loading...

Naga Tuma
Member+
Posts: 5523
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: Ethiopia Vote Agency Queries Key Opposition Leader’s Citizenship [Bloomberg]

Post by Naga Tuma » 12 Feb 2020, 22:12

ወይ ዘንድሮ፣ የዜግነት ትግል ያልገባዉ ለሃገር ታጋይ ነኝ ባይ እና ወሬ ሱሴ ብሎ የቀረዉን ታሳየን ጀመር?

Revelations
Senior Member+
Posts: 33713
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: Ethiopia Vote Agency Queries Key Opposition Leader’s Citizenship [Bloomberg]

Post by Revelations » 12 Feb 2020, 23:11

ወቸው ጉድ! "እህህ ዘውዴ ስላስምሽ ነጋ" አለ ሰውየው:: የብርቱኬ ስራ ጨመረ ማለት ነው! :lol: :lol: :lol:
Please wait, video is loading...


Revelations
Senior Member+
Posts: 33713
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: Ethiopia Vote Agency Queries Key Opposition Leader’s Citizenship [Bloomberg]

Post by Revelations » 13 Feb 2020, 07:57

Please wait, video is loading...

Revelations
Senior Member+
Posts: 33713
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: Ethiopia Vote Agency Queries Key Opposition Leader’s Citizenship [Bloomberg]

Post by Revelations » 13 Feb 2020, 17:45

Please wait, video is loading...

Sam Ebalalehu
Member
Posts: 3639
Joined: 23 Jun 2018, 21:29

Re: Ethiopia Vote Agency Queries Key Opposition Leader’s Citizenship [Bloomberg]

Post by Sam Ebalalehu » 13 Feb 2020, 18:09

It is a bizzare argument. He could argue why pick on me. Berhanu also should be forbidden to participate in Ethiopian politics. It is inane however to argue because we two do not have Ethiopian citizenships, we both should be allowed to participate in Ethiopian politics. The guy does not seem to have a common sense let alone a rational thinking.
The comparison however is not legit. Berhanu used, if he does, the Eritrean passport for travel. Many political leaders used foreign passports just for travel purposes because they cannot get one from their own government which they struggle to unseat.
Meles allegedly used the Somali passport when he was the rebel leader. But the Somali government did not confer Somali citizenship to him. I was in Sudan when Seyoum of TPLF used to fly to Europe and America almost every other month , most probably using a Sudan passport, but, as far as I know, he had never been a Sudanese national.
Jawar, it is time to make a rational argument that at least a six grader could offer.

Post Reply