Page 1 of 1

በአማራ ክልል ራያ አላማጣ ዛታ እና ኦፍላን ጨምሮ አወዛጋቢ አካባቢዎች ባሉ አማራ ማኅበረሰብ ላይ እየደሰ ያለው ግፍ በእጅጉ እንዳሳሰባቸው የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ገለጹ

Posted: 03 May 2024, 13:38
by Za-Ilmaknun
በአማራ ክልል ራያ አላማጣ ዛታ እና ኦፍላን ጨምሮ አወዛጋቢ በሆኑት አካባቢዎች ባሉ አማራ ማኅበረሰብ ላይ በትግራይ የታጠቁ ኃይሎች እየደሰ ያለው ግፍ በእጅጉ እንዳሳሰባቸው የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ ማሐማት ገለጹ።

የአማራ እና የትግራይ ክልሎች በይገባኛል በሚወዛገቡባቸው አካባቢዎች ካለፈው ሳምንት ጀምሮ የታጠቁ ኃይሎች እየገቡ መሆናቸውን በመግለጽ ነዋሪዎች እየሸሹ መሆናቸው መዘገቡ ይታወቃል።

ለሁለት ዓመት የቆየውን ደም አፋሳሽ ጦርነት ለማስቆም ያስቻለውን የፕሪቶሪያውን ስምምነት ተከትሎ ከአወዛጋቢዎቹ አካባቢዎች ከፌደራል መንግሥቱ ኃይሎች ውጪ ያሉ ታጣቂዎች ለቀው እንደሚወጡ የተገለጸ ሲሆን፣ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ የተለያዩ መረጃዎች ከአካባቢዎቹ ነዋሪዎች እየወጡ ነው።

ቢቢሲ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች እና የአካባቢዎቹ ባለሥልጣናት እንደሚሉት በከተሞች አካባቢ የፌደራል ፖሊስ እና የመከላከያ ሠራዊት አባላት መሠማራታቸውን፣ ከከተሞች ውጪ ባሉ ቦታዎች ላይ ደግሞ የህወሓት ታጣቂዎች እንደሚታዩ ገልጸዋል።

ይህንንም ተከትሎ በምሥራቅ በኩል በሚገኙት አወዛጋቢ ቦታዎቹ ይገኙ የነበሩ ነዋሪዎች በተፈጠረባቸው ስጋት ምክንያት መኖሪያቸውን ለቀው ወደ አጎራባች የአማራ ክልል አካባቢዎች መፈናቀላቸው ተነግሯል።

በዚህም ሳቢያ ከአላማጣ ከተማ፣ ዛታ እና ኦፍላ የራያ ወረዳዎች የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር 50 ሺህ መድረሱን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ እርዳታ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ከቀናት በፊት አስታውቋል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cx9wxyxkpxeo

Re: በአማራ ክልል ራያ አላማጣ ዛታ እና ኦፍላን ጨምሮ አወዛጋቢ አካባቢዎች ባሉ አማራ ማኅበረሰብ ላይ እየደሰ ያለው ግፍ በእጅጉ እንዳሳሰባቸው የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ገለጹ

Posted: 03 May 2024, 13:42
by Za-Ilmaknun
A few weeks ago, the TPLF forces launched an extensive military operation in the south taking control of at least four districts in Alamata and Koreas of Ethiopia. In an interview with BBC, Getachew Reda, head of the interim administration of Tigray, denied that it is the TPLF or the regional government that undertook the military operation. The military operation has been rather presented as the works of “those who are hostile to the Pretoria Agreement,” – something that is not clearly spelled out as to who that entity is. :mrgreen:

According to OCHA, more than 50,000 civilians were displaced from the area after the TPLF’s latest military action and found themselves in Kobo, Wolida and Sekota.