Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
MINILIK SALSAWI
Member+
Posts: 9499
Joined: 24 Aug 2012, 12:02

ዝቋላ ድጋሚ ሥጋት ገጥሞታል

Post by MINILIK SALSAWI » 25 Mar 2024, 03:06

በቅርቡ መነኮሳቱ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉበት የደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም መጠነኛ ጥበቃ ሲሰጠው የነበረው መከላከያ ትናንት እሑድ ገዳሙን ለቅቆ በመውጣቱ ድጋሚ ሥጋት ላይ መውደቁን የተላከልን መረጃ ያመለክታል።

ከዚህ በፊት ከመንግሥት ጋር በነበሩት ውይይቶች ገዳሙ ከሥጋት ነጻ የሚሆንበት ሥራ እንደሚሠራ ስምምነት ላይ መደረሱ የሚታወስ ሲሆን ምክንያቱ ለጊዜው ግልጽ ባልሆነበት ሁኔታ የመከላከያ ሠራዊቱ በምሽት ገዳሙን ለቅቆ መውጣቱ ማኅበረ መነኮሳቱ ላይ ከፍተኛ ሥጋት ፈጥሯል።

"የሚመለከታቸው አካላት አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጡ እናሳስባለን" ብሏል ገዳሙ።