-
- Senior Member+
- Posts: 30996
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
HERE IS WHY! I Hope now you can understand what I have been talking about! የሴም፣ የግሪክ፣ የሮማ ስልጣኔዎች ሁሉ እናት ጥንታዊ የግብጽ ስልጣኔ ናትና
-
- Member+
- Posts: 5549
- Joined: 24 Apr 2007, 00:27
Re: የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
Horus:
Advice received. Thank you for sharing it.
Let me reciprocate below.
ሲቆርሱ ኣያሳንሱ ኣታድርገዉ እና, do you have any instance when Naga Tuma failed to understand or didn’t know the point you made here?
ሞረ ኣንባቢዉ ነጋ ቱማ የፊደልን አሻራ ኣስተዉሎ ለቆንቆኣችን ወይም ቋንቋችን መጠቀም እና እንጠቀም ማለት ከጀመረ ሰንብቷል።
ኦሮሞእንዴክስ የተባለ ፎረም ላይ ፍደለ ሳባ ቤክቱ የሚል ርዕስ እስከ መጀመር የደረሰዉ ኣንተ መፈጠርህን ሳያዉቅ በፊት ነበር።
That said, I also have a novel suggestion for you.
I remember reading you and Abe Abraham discussing about the history of Fidel as experts.
This clip doesn’t even scratch the surface of ሀ ግዕዝ፣ ሁ ካዕብ፣ ሂ ሳልስ፣ … and አቡጊዳ።
My novel suggestion is that if you both or people that you know to be experts like you work on them, a lot of academic papers are likely to come out of them in the years to come.
An additional novel suggestion is to start a fitting journal for it in order to avoid the constraints of established journals like Nature and Science.
I say constraints based on my own personal experience. I once sent an article to an established journal. Its editor understood it and said his journal is not appropriate for it. He suggested that it has a novel idea that I consider sending it to Science. Both Science and Nature rejected it. Time will tell whether the editor who made the recommendation or the editors of Nature and Science who rejected it were correct to do so.
To get out of that kind of constraint, I tried to launch my own journal that will someday parallel both Nature and Science. Why not? It failed to go far because of my own constraints.
If mine couldn’t take off so far, it doesn’t mean yours wouldn’t be able to take off.
-
- Member+
- Posts: 6476
- Joined: 14 Feb 2021, 15:24
Re: የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
Horus,
You don't fail to disappoint me over and over again
You are one stupidest graduate of white schools
This video is nothing but a complete lie!
We know where the letters came from, Ethiopia- Amharic!!!!. We teach our kids the truth. We have the truth.
Horus, it so'cks you cant even teach your kids the truth because you don't know it. All you know is what the white man told you,
You even follow that Indian guy for political directions
You don't fail to disappoint me over and over again
You are one stupidest graduate of white schools
This video is nothing but a complete lie!
We know where the letters came from, Ethiopia- Amharic!!!!. We teach our kids the truth. We have the truth.
Horus, it so'cks you cant even teach your kids the truth because you don't know it. All you know is what the white man told you,
You even follow that Indian guy for political directions
-
- Senior Member+
- Posts: 30996
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Re: የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
ትክክል ነህ ፤ ይህ ፈረንጅ የላቲን አልፋቤቶች ከግብጽ ሃይሮ ግሊፊክስ (ቅዱስ ጽሁፍ) መምጣቱን እንጂ የኢትዮጵያ ግዕዝ (ቅዱስ) ፊደል እንዴት እንደ መጣ አያወራም። ስለዚያ ማወቅ ያለብን እኛ ነን ። ይህን መልክት ላንተ የላኩት አፋን ኦርሞ በፊደል መጻፍ አለበት ብለህ ኦሮሞ ወንሞችን ስታስተምር ወይም ስትሟገት ስለማላቅ ነው። የላቲን አልፋቤታ ከፊድል እጅግ ያነሰ እንደ ሆነ ላሳይ ብዬ ነው ። በእጅ ያለ ወርቅ ከመዳብ ይቆጠራል ይባል የለ!
-
- Senior Member+
- Posts: 30996
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Re: የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
Union,
ስድብ እውቀት አይደልም፣ የድንቁርናን መሸፈኛ ነው። ያጠናሃውና ለምታምነው ነገር ፋክት ካልህ እስቲ እንየው?
ስድብ እውቀት አይደልም፣ የድንቁርናን መሸፈኛ ነው። ያጠናሃውና ለምታምነው ነገር ፋክት ካልህ እስቲ እንየው?
-
- Member+
- Posts: 6476
- Joined: 14 Feb 2021, 15:24
-
- Member+
- Posts: 6476
- Joined: 14 Feb 2021, 15:24
Re: የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
Regarding the question you asked me, it's obvious at this point that Geez writing is not what we have now, but Amharic. If you look at the monuments of Axum, you will see Geez writting but an Amharic speaking person would not understand it, that is because what's on the monuments is Geez, not Amharic.
When Alexander the great copied it Geez already have died and was only been used in the churches. So he did not copy Geez but Amharic alphabets!
When Alexander the great copied it Geez already have died and was only been used in the churches. So he did not copy Geez but Amharic alphabets!
-
- Senior Member
- Posts: 12373
- Joined: 22 Feb 2014, 16:46
Re: የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
Horus,
Here's my golden advice: Since you are so super intelligent and creative, use that same energy that you use to condescendingly advise Oormos & others, for the benefit of your Gurage people. They need your brain to help uplift themselves out of poverty, under-development, etc.
Us Oromos will be just fine without the advice of an individual who happens to harbor deep-seated hatred & fear of us. Thanks!
Here's my golden advice: Since you are so super intelligent and creative, use that same energy that you use to condescendingly advise Oormos & others, for the benefit of your Gurage people. They need your brain to help uplift themselves out of poverty, under-development, etc.
Us Oromos will be just fine without the advice of an individual who happens to harbor deep-seated hatred & fear of us. Thanks!
-
- Senior Member+
- Posts: 30996
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Re: የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
በል ይመችህ! ጉራጌ የፊደል ችግር የለበትም ! ግን ግዕዝ ፊደል የላቲን አልፋቤታ አባት እንደ ሆነ እወቅ፤ በላቲን መጻፍ ስልጡን አያደርግም! ስላም!Sadacha Macca wrote: ↑28 Feb 2024, 18:02Horus,
Here's my golden advice: Since you are so super intelligent and creative, use that same energy that you use to condescendingly advise Oormos & others, for the benefit of your Gurage people. They need your brain to help uplift themselves out of poverty, under-development, etc.
Us Oromos will be just fine without the advice of an individual who happens to harbor deep-seated hatred & fear of us. Thanks!
-
- Senior Member
- Posts: 12373
- Joined: 22 Feb 2014, 16:46
Re: የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
Horus wrote: ↑28 Feb 2024, 21:47በል ይመችህ! ጉራጌ የፊደል ችግር የለበትም ! ግን ግዕዝ ፊደል የላቲን አልፋቤታ አባት እንደ ሆነ እወቅ፤ በላቲን መጻፍ ስልጡን አያደርግም! ስላም!Sadacha Macca wrote: ↑28 Feb 2024, 18:02Horus,
Here's my golden advice: Since you are so super intelligent and creative, use that same energy that you use to condescendingly advise Oormos & others, for the benefit of your Gurage people. They need your brain to help uplift themselves out of poverty, under-development, etc.
Us Oromos will be just fine without the advice of an individual who happens to harbor deep-seated hatred & fear of us. Thanks!
If you can make the original post in English, then you should be able to reply to any feedback in English as well.
-
- Member+
- Posts: 5549
- Joined: 24 Apr 2007, 00:27
Re: የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
ሆረስ፥
ያስተዋልኩትን ለማካፈል ኦሮሞእንዴክስ የተባለ ፎረም ላይ ፍደለ ሳባ ቤክቱ ብዬ ኣዲስ የዉይይት ርዕስ የጀመርኩኝ ኣንተ መፈጠርህን ሳላዉቅ በፊት ነበር ያልኩኝን ኣነበብክ?
እኔ ከሁሉ በላይ ያደነኩኝ ሃገር በቀልነቱን ነዉ።
ለዚህ ነዉ ለምናገራቸዉ ሁለት የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ፊደልን የምጠቀመዉ።
እኔ ማንንም እንደ እኔ ካልተጠቀማችሁ ብዬ ማዘዝ ኣልችልም። መብቱም ዬለኝም። ማንም ኣትጠቀም ብሎ እንድያዘኝ ኣልፈልግም። አስተሳሰቤ ያን ያህል ቀላል ነዉ።
እኔ የፊደልን ታሪክ ኣስተዉዬ እጠቀማለሁ ስል ዩንየን ግብጢ ኬኘ እያለ ላቲን ይመቸኛል ካለ እኔ ልምከረዉ?
-
- Member+
- Posts: 5549
- Joined: 24 Apr 2007, 00:27
Re: የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
ሆረስ፥
ይህ ታሪክ ኢትዮጵያ ዉስጥ በሰፊዉ መታወቅ ያለበት ነዉ።
በቅርቡ የጠየኩትን ጥያቄ እዚህም ልጠይቅ።
ኢትዮጵያ ምን ያህል ጥንታዊ እንደሆነች ለማወቅ የሚከተሉትን አምስት ቃላት ማወቅ ኣይበቃም፧?
ጎፍታ ጎይታ ጌታ ጎድ
አባ ኣብ አባት አቡ
ሰበ ሰብ ሻብያ
ዌረረ ወረራ ዋር
ሴረ ሴራ ሸርያ
እነዚህ አምስት ቃላት ምን ያህል ኢትዮጵዊያን አፍ መፍቻ ቋንቋዎች ዉስጥ የጋራ ሆነዉ ይታወቃሉ? ግምት ኣለህ? የማይታወቁበት ሌሎች የኢትዮጵያ አፍ መፍቻ ቋንቋዎች ዉስጥ በምን ቃላት ይታወቃሉ? እነሱም ብሄረሰብ ሳይሆኑ ቤተሰብ ናቸዉ።
እነዚህን ቃላት ከመዋዕለ ሕፃናት ጀምሮ ማስተማር ኣይቻልም? በትምህርት ምንስቴር መሪነት?
ለኢትዮጵያ ህዳሴ ወይም ግስጋሴ ያልኩኝ መሠረቱ ኣንዱ ይህ ነዉ እኮ።
ይህ ታሪክ ኢትዮጵያ ዉስጥ በሰፊዉ መታወቅ ያለበት ነዉ።
በቅርቡ የጠየኩትን ጥያቄ እዚህም ልጠይቅ።
ኢትዮጵያ ምን ያህል ጥንታዊ እንደሆነች ለማወቅ የሚከተሉትን አምስት ቃላት ማወቅ ኣይበቃም፧?
ጎፍታ ጎይታ ጌታ ጎድ
አባ ኣብ አባት አቡ
ሰበ ሰብ ሻብያ
ዌረረ ወረራ ዋር
ሴረ ሴራ ሸርያ
እነዚህ አምስት ቃላት ምን ያህል ኢትዮጵዊያን አፍ መፍቻ ቋንቋዎች ዉስጥ የጋራ ሆነዉ ይታወቃሉ? ግምት ኣለህ? የማይታወቁበት ሌሎች የኢትዮጵያ አፍ መፍቻ ቋንቋዎች ዉስጥ በምን ቃላት ይታወቃሉ? እነሱም ብሄረሰብ ሳይሆኑ ቤተሰብ ናቸዉ።
እነዚህን ቃላት ከመዋዕለ ሕፃናት ጀምሮ ማስተማር ኣይቻልም? በትምህርት ምንስቴር መሪነት?
ለኢትዮጵያ ህዳሴ ወይም ግስጋሴ ያልኩኝ መሠረቱ ኣንዱ ይህ ነዉ እኮ።
-
- Senior Member+
- Posts: 30996
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Re: የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
ናጋ ቱማ፣
አማርኛ መጠቀምክን ፣ በፊደል መጻፍን አደግፋለሁ ፣አከብራለሁም ። የኢትዮጵያ ቋንቋዎችኮ የአፍሮ ኤሺያቲክ ቋንቋዎች ሁሉ አባቶች ናቸው ሲባል በምርምር ላይ የተመሰረተ መሆኑ የታወቀ ነው ። እኔ ከ30 አመት በላይ ባደረጉት ጥናት ክ20% እስከ 30% ፕሮቶ ኢንዶ ኢሮፒያን ኢቲሞሎጂ ግዕዝ ወይም ኢቲዮፒክ ናቸው ስል ብዙ አመት ነው ። እንተም እንዳልከው ብዙ ኦሪታዊ የሆኑ ቃላት አይደለም በኦሮሞፋና ግ ዕዝ ከላቲን ጋር አንድ ናቸው ። ለምሳሌ ጂን፣ ጽንስ፣ ጂኒሲስ፣ ጥንስስ ፣ ግንድ ፣ ጥንት ፣ ገና ወዘተ ሁሉም አንድ ናቸው ፣ ልደት፣ ፍጥረት፣ ወይም መጀመሪያ ማለት ነው ። አው ጌታ፣ ጎድ፣ ጎይታ፣ ጊታ ሁሉም አንድ ናቸው።
እኔ ከኦሮሞ ኢሊቶች ጋር ያለኝ ጠብ ከኢትዮጵያ ስልጣኔ የተለየ መሰረት እንዳለው ሕዝብ አጠገባቸው ያለውን ታሪካና ቋንቋ እየተሁ የሌላቸው በልብ ወለድ ለመፍጠር የሚያደርጉት ጥረት ነው ። ከንቱ ግዜ ማጥፋት ስለሆነ ኦሮሞኛ በግዕዝ ፊደል ተጽፎ ቢሆን ለለፉት 30 አመት ቋንቋው የት በደረሰ! ዛሬ ከጥቂት የቁቤ ትውልድ በተቀር ማንም በላቲን የተጻፈን ኦሮሞኛ እንደ ማያነብ ታውቃለህ ። ስለዚህ ዛሬም ቢሆን ኦሮሞኛ ኦራል ቋንቋ እንጂ የስነ ጽሁፍ ቋንቋ አይደለም ። ያ ደሞ የኦሮሞ ብሄረተኞች ላቲን ቁቤ አባዜ ስህተት ነው ። ያ ነው የኔ ሂስ!
አማርኛ መጠቀምክን ፣ በፊደል መጻፍን አደግፋለሁ ፣አከብራለሁም ። የኢትዮጵያ ቋንቋዎችኮ የአፍሮ ኤሺያቲክ ቋንቋዎች ሁሉ አባቶች ናቸው ሲባል በምርምር ላይ የተመሰረተ መሆኑ የታወቀ ነው ። እኔ ከ30 አመት በላይ ባደረጉት ጥናት ክ20% እስከ 30% ፕሮቶ ኢንዶ ኢሮፒያን ኢቲሞሎጂ ግዕዝ ወይም ኢቲዮፒክ ናቸው ስል ብዙ አመት ነው ። እንተም እንዳልከው ብዙ ኦሪታዊ የሆኑ ቃላት አይደለም በኦሮሞፋና ግ ዕዝ ከላቲን ጋር አንድ ናቸው ። ለምሳሌ ጂን፣ ጽንስ፣ ጂኒሲስ፣ ጥንስስ ፣ ግንድ ፣ ጥንት ፣ ገና ወዘተ ሁሉም አንድ ናቸው ፣ ልደት፣ ፍጥረት፣ ወይም መጀመሪያ ማለት ነው ። አው ጌታ፣ ጎድ፣ ጎይታ፣ ጊታ ሁሉም አንድ ናቸው።
እኔ ከኦሮሞ ኢሊቶች ጋር ያለኝ ጠብ ከኢትዮጵያ ስልጣኔ የተለየ መሰረት እንዳለው ሕዝብ አጠገባቸው ያለውን ታሪካና ቋንቋ እየተሁ የሌላቸው በልብ ወለድ ለመፍጠር የሚያደርጉት ጥረት ነው ። ከንቱ ግዜ ማጥፋት ስለሆነ ኦሮሞኛ በግዕዝ ፊደል ተጽፎ ቢሆን ለለፉት 30 አመት ቋንቋው የት በደረሰ! ዛሬ ከጥቂት የቁቤ ትውልድ በተቀር ማንም በላቲን የተጻፈን ኦሮሞኛ እንደ ማያነብ ታውቃለህ ። ስለዚህ ዛሬም ቢሆን ኦሮሞኛ ኦራል ቋንቋ እንጂ የስነ ጽሁፍ ቋንቋ አይደለም ። ያ ደሞ የኦሮሞ ብሄረተኞች ላቲን ቁቤ አባዜ ስህተት ነው ። ያ ነው የኔ ሂስ!
-
- Member+
- Posts: 5549
- Joined: 24 Apr 2007, 00:27
Re: የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
ኢትዮጵያ የኮሌጅ ተማሪ ሆኜ ኣንጋፋ የኢትዮጵያ ምሁራን ወይም ሳይንቲስቶች የተባሉ ሶስት ስሞችን ኣስታዉሳለሁ።
ዶክተር ጌታቸዉ ቦለዳ
ዶክተር አክሊሉ ለማ
ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ
ፕሮፌሰር አስራት ወደ ፖለትካ ከገባ በኋላ ስለፊደል ተናግሮ ነበር የሚል ወሬ ኣስታዉሳለሁ።
ፕሮፌሰሩ ስለ ፊደል የተናገረዉ የተቀመጠ ወይም የሚታወስ ኣለ?
ሆረስ፥
ይህን ጥያቄ ለመጠየቅ ወደዚህ ርዕስ ኣሁን ተመልሼ ነዉ መልስህን እና ሂስህን ያየሁኝ። እመለስበታለሁ።
ዶክተር ጌታቸዉ ቦለዳ
ዶክተር አክሊሉ ለማ
ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ
ፕሮፌሰር አስራት ወደ ፖለትካ ከገባ በኋላ ስለፊደል ተናግሮ ነበር የሚል ወሬ ኣስታዉሳለሁ።
ፕሮፌሰሩ ስለ ፊደል የተናገረዉ የተቀመጠ ወይም የሚታወስ ኣለ?
ሆረስ፥
ይህን ጥያቄ ለመጠየቅ ወደዚህ ርዕስ ኣሁን ተመልሼ ነዉ መልስህን እና ሂስህን ያየሁኝ። እመለስበታለሁ።
-
- Senior Member+
- Posts: 30996
- Joined: 19 Oct 2013, 19:34
Re: የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
ስለ ፕሮፍ ጌታቸው ቦሎዲያ ይህውNaga Tuma wrote: ↑23 Mar 2024, 23:39ኢትዮጵያ የኮሌጅ ተማሪ ሆኜ ኣንጋፋ የኢትዮጵያ ምሁራን ወይም ሳይንቲስቶች የተባሉ ሶስት ስሞችን ኣስታዉሳለሁ።
ዶክተር ጌታቸዉ ቦለዳ
ዶክተር አክሊሉ ለማ
ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ
ፕሮፌሰር አስራት ወደ ፖለትካ ከገባ በኋላ ስለፊደል ተናግሮ ነበር የሚል ወሬ ኣስታዉሳለሁ።
ፕሮፌሰሩ ስለ ፊደል የተናገረዉ የተቀመጠ ወይም የሚታወስ ኣለ?
ሆረስ፥
ይህን ጥያቄ ለመጠየቅ ወደዚህ ርዕስ ኣሁን ተመልሼ ነዉ መልስህን እና ሂስህን ያየሁኝ። እመለስበታለሁ።
ዶ/ር አክሊሉ ለማ ሳይንቲስት እንጂ ሊንጉዊስት አልነበረም ። የቋንቋ ሊቁ ሎሬት መንግስቱ ለማ ነው ።
ፕሮፍ አስራት ወልደየስ ሃኪምና የሜዲሲን ፕሮፌስር እንጂ ሊንጉዊስት አልነበሩም ። የግዕዝና ቋንቋ ሊቆቹ ፕሮፍ ጌታቸው ኃይሌ (ፊሎሎጊስት ከጀርመን) እና ዶ/ርስርጉው ሃብተ ስላሴ
(ከጀርመን)። ከዚህ ባለፈ የግዕዝ አገር በቀል ግዙፋ እንደነ ከሳቴ ብርሃን ያሉት የቤተ ክህነት ሊቃውንት እጅግ ብዙ ናቸው
-
- Senior Member
- Posts: 11886
- Joined: 04 Aug 2018, 13:15
Re: የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
<> ቦለዲያ ሲያወራና ሲቀልድ ኖሮ አንዲት ፅሁፍ እንኳን ሳያሳትም ያለፈ ትምባኋም ነበረ።
-
- Member+
- Posts: 5549
- Joined: 24 Apr 2007, 00:27
Re: የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
ሆረስ፥Horus wrote: ↑24 Mar 2024, 01:20ስለ ፕሮፍ ጌታቸው ቦሎዲያ ይህውNaga Tuma wrote: ↑23 Mar 2024, 23:39ኢትዮጵያ የኮሌጅ ተማሪ ሆኜ ኣንጋፋ የኢትዮጵያ ምሁራን ወይም ሳይንቲስቶች የተባሉ ሶስት ስሞችን ኣስታዉሳለሁ።
ዶክተር ጌታቸዉ ቦለዳ
ዶክተር አክሊሉ ለማ
ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ
ፕሮፌሰር አስራት ወደ ፖለትካ ከገባ በኋላ ስለፊደል ተናግሮ ነበር የሚል ወሬ ኣስታዉሳለሁ።
ፕሮፌሰሩ ስለ ፊደል የተናገረዉ የተቀመጠ ወይም የሚታወስ ኣለ?
ሆረስ፥
ይህን ጥያቄ ለመጠየቅ ወደዚህ ርዕስ ኣሁን ተመልሼ ነዉ መልስህን እና ሂስህን ያየሁኝ። እመለስበታለሁ።
ዶ/ር አክሊሉ ለማ ሳይንቲስት እንጂ ሊንጉዊስት አልነበረም ። የቋንቋ ሊቁ ሎሬት መንግስቱ ለማ ነው ።
ፕሮፍ አስራት ወልደየስ ሃኪምና የሜዲሲን ፕሮፌስር እንጂ ሊንጉዊስት አልነበሩም ። የግዕዝና ቋንቋ ሊቆቹ ፕሮፍ ጌታቸው ኃይሌ (ፊሎሎጊስት ከጀርመን) እና ዶ/ርስርጉው ሃብተ ስላሴ
(ከጀርመን)። ከዚህ ባለፈ የግዕዝ አገር በቀል ግዙፋ እንደነ ከሳቴ ብርሃን ያሉት የቤተ ክህነት ሊቃውንት እጅግ ብዙ ናቸው
ስሞቻቸዉን የሰማሁ አንጋፋ የኢትዮጵያ ምሁራን ወይም ሳይንቲስቶች ኣልኩኝ እንጂ ሊንጉዊስቶች ነበሩ ብያለሁ?
ለክሊፑ ኣመሰግናለሁ።
-
- Member+
- Posts: 5549
- Joined: 24 Apr 2007, 00:27
-
- Member+
- Posts: 5549
- Joined: 24 Apr 2007, 00:27
Re: የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
ሆረስ፥Horus wrote: ↑01 Mar 2024, 17:12ናጋ ቱማ፣
አማርኛ መጠቀምክን ፣ በፊደል መጻፍን አደግፋለሁ ፣አከብራለሁም ። የኢትዮጵያ ቋንቋዎችኮ የአፍሮ ኤሺያቲክ ቋንቋዎች ሁሉ አባቶች ናቸው ሲባል በምርምር ላይ የተመሰረተ መሆኑ የታወቀ ነው ። እኔ ከ30 አመት በላይ ባደረጉት ጥናት ክ20% እስከ 30% ፕሮቶ ኢንዶ ኢሮፒያን ኢቲሞሎጂ ግዕዝ ወይም ኢቲዮፒክ ናቸው ስል ብዙ አመት ነው ። እንተም እንዳልከው ብዙ ኦሪታዊ የሆኑ ቃላት አይደለም በኦሮሞፋና ግ ዕዝ ከላቲን ጋር አንድ ናቸው ። ለምሳሌ ጂን፣ ጽንስ፣ ጂኒሲስ፣ ጥንስስ ፣ ግንድ ፣ ጥንት ፣ ገና ወዘተ ሁሉም አንድ ናቸው ፣ ልደት፣ ፍጥረት፣ ወይም መጀመሪያ ማለት ነው ። አው ጌታ፣ ጎድ፣ ጎይታ፣ ጊታ ሁሉም አንድ ናቸው።
እኔ ከኦሮሞ ኢሊቶች ጋር ያለኝ ጠብ ከኢትዮጵያ ስልጣኔ የተለየ መሰረት እንዳለው ሕዝብ አጠገባቸው ያለውን ታሪካና ቋንቋ እየተሁ የሌላቸው በልብ ወለድ ለመፍጠር የሚያደርጉት ጥረት ነው ። ከንቱ ግዜ ማጥፋት ስለሆነ ኦሮሞኛ በግዕዝ ፊደል ተጽፎ ቢሆን ለለፉት 30 አመት ቋንቋው የት በደረሰ! ዛሬ ከጥቂት የቁቤ ትውልድ በተቀር ማንም በላቲን የተጻፈን ኦሮሞኛ እንደ ማያነብ ታውቃለህ ። ስለዚህ ዛሬም ቢሆን ኦሮሞኛ ኦራል ቋንቋ እንጂ የስነ ጽሁፍ ቋንቋ አይደለም ። ያ ደሞ የኦሮሞ ብሄረተኞች ላቲን ቁቤ አባዜ ስህተት ነው ። ያ ነው የኔ ሂስ!
ይህ ዉይይት ጠቃሚም ኣስፈላጊም ነዉ።
የቦረና እና ግዕዝ ዲክሽነሪ ያስፈልገናል ካልኩኝ ሰንብቻለሁ።
የሃገራችን ኦሪታዊ የቋንቋ ታሪክ ከዛ በላይ የምያብራራ ዲክሽነሪ ሊኖር የሚችል ኣይመስለኝም።
ከኣሁን በፊት ስለቦረና ቋንቋ ታሪክ ክፉኛ ወቅሰሀኝ ነበር። የቋንቋዉ ተናጋሪ ስላልሆንክ ነዉ ብዬ ኣለፍኩኝ። ይህ ማብራርያህ የንን ወቀሳህን ይሽራል።
ብታዉቀዉ ግዕዝን ወደህ የቦረናን ቋንቋ ኣለመዉደድ የምትችል ኣይመስለኝም።
ፊደልን ስለመጠቀም ሂስህ ተገቢ ነዉ። እንደ እኔ አስተሳሰብ ኣንገብጋቢም ነዉ።
ኣስፈላጊነቱን በራሴ ኣስተዉዬ እዚሁ ፎረም ላይ የዉይይት ርዕስ ጀምሬ ነበር። ስለሚመጣዉ ኬኛ ኣብዮት፣ እንደ ቀልድ።
ኣንገብጋቢነቱ የፊደል ፈጠራ ምልክትነት ነዉ።
የፊደል ምልክትነት ተፈጥሮኣዊ ወይም ናቹራል የነበረ ይመስለኛል።
ተፈጥሮኣዊ ወይም ናቹራል የነበረ ከሆነ ቀጥሎ የሚመጣዉ ጥያቄ ምልክቶቹን የፈጠሩት ይናገሩ የነበረዉ ቋንቋ የትኛዉ ነበረ ነዉ?
ቁልፍ ጥያቄ ነዉ። ኣይዴለም?
ቦረና እና ግዕዝ ኦሪታዊ የነበሩ ከሆነ ፊደልን እንደ ምልክት የቀረጹት ምናልባትም ዛሬ የቦረና ቋንቋ የምንለዉን ይናገሩ ወይም የምያዉቁ የነበሩ ይሆን? በሌላ አነጋገር ጎፍታ፣ አባ፣ ሰበ፣ ዌረረ፣ ሴረ ማለትን የምያዉቁ የነበሩ ይሆን?
በል እንግዲህ ሳይንስ ኣእምሮን ስያንኳኳ ኣልሰማሁም ብሎ የሚንጣጣን ኤሊት ነዉ በለኛ።
ተፈጥሮኣዊ ወይም ናቹራል የሆነ ፊደል እያለ ያልሆነን መጠቀም የቋንቋዉ እድገት ላይ ተፅዕኖ ሊኖረዉ እንደሚችል እኔም ኣስተዉዬ የጀመርኩት ርዕስ ዉስጥ ጽፌያለሁ።
ኣንድ በጣም ቀላል ምሳሌ ልጥቀስልህ።
ሂስ በቦረና ቋንቋ ኮሜ ወይም ኮሚ ለሚባሉ ቃላት ይቀርባል። ኮሜ እና ኮሚ ልዩነታቸዉ በፊደል እየጻድኩኝ እያለሁ ነዉ ግልጥ ያለልኝ።
ኣማርኛ ዉስጥ ቃላት ተጣምረዉ ኣንድ ቃል እንደሚሆኑት ኦሮምኛ ዉስጥም ቃላት ተጣምረዉ ኣንድ ቃል ይሆናሉ።
አማርኛ ዉስጥ ለምሳሌ ኣልኩ፣ ኣልኩት፣ ኣልኳት የተጣመሩ ቃላት ናቸዉ። በእንግሊዘኛ ቢሆን ኣይ ሴይድ፣ ኣይ ሴይድ ቱ ህም፣ ኣይ ሴይድ ቱ ሄር ይሆናሉ። ኣይዴለም?
ኮሜን እና ኮሚን በፊደል እያጻፍኩ የትኛዉ ነዉ ትክክል ብዬ ሳማርጥ የተለያየ ትርጉም ሊኖራቸዉ እንደሚችል ግልጽ ሆነልኝ። ኮሜ የተናጋሪዉ ስሞታ፣ ኮሚ የሌላ ተናጋሪ ስሞታ ማለት መሆንን ኣስተዋልኩኝ። በአማርኛ ቢሆን ኮሜ ስሞታዬ፣ ኮሚ የሌላ ወይም የሌሎች ስሞታ ይሆናሉ። ማስተዋሌ ትክክል ከሆነ።
ያ ደግሞ የ ሀ ግዕዝ፣ ሁ ካዕብ፣ ሂ ሳልስ፣ ወዘተን አመጣጥ ኣስጠየቀኝ።
ይህ ምንን ያመለክታል? ተፈጥሮኣዊ የሆነን ፊደል ለኦሪታዊ ቋንቋ መጠቀም ቋንቋዉን በኣጭር ግዜ ዉስጥ ያለመልማል።
ተሳሳትኩ? እስቲ የቱ ጋ?
-
- Senior Member
- Posts: 11886
- Joined: 04 Aug 2018, 13:15
Re: የፊደል ታሪክ! HORUS'S GOLDEN ADVICE TO NAGA TUMA: WRITE YOUR LANGUAGE IN FIDEL
<> ልጁ ጠበቃ ስለሆነች ብዙ ባላወራ ይሻላል፣ ግን ሰውዬው አዋቂ ግን ሰነፍ ነበር።