Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Meleket
Member
Posts: 3057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ስነፍጥረትን ለማነጋገር የበቃ ኤርትራዊ የጥበብ ሰው - የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) - በስንኞቹ ሲዘከር

Post by Meleket » 30 Aug 2023, 10:28

ደሓን ሕደሪ ፀሓይ

ደሓን ሕደሪ ፀሓይ፡ ክሳብ ጽባሕ ንግሖ፡ /2/
ደሓን ሕደሪ ፀሓይ፡ ክሳብ ጽባሕ ንግሖ፡ /2/
ኣብ ሃዋህው ክሕምብስንጸልማት ክንጋልሖ፡ /2/
ምስ ወርሒ ከማሲ ምስ ከዋክብቲ ከውግሖ።

ምሳኽን’የ ንኣኽን’የ ዝዛረብ ዘለኹ ስምዓኒ ከዋኽብቲ፡
ኣይረኣክናኣን ዲኽን ክትሓልፍ ብለይቲ፡
ሕይወት ዘለዋ ቆጽሊ’ያ ጽብቕቲ ለምለም ሰቲ።


ደሓን’ዶ ሓዲርኻ ኾኸብ ጽባሕ ናይ ወጋሕታ፡ /2/
ብህልፋት ንጉሆ ናይ ፀሓይ መጀመርታ፡
ኣየፋነካያን ዲኻ . . . . . . . . ።* /2/

ተሓቢረ ክከይድ ክስዕብ ኣሰራ፡ ኣነ ክስዕብ ኣሰራ፡ /2/
ዝፈትዋ ቃልኪዳነይ ናብ ዘላቶ ስፍራ፡ /2/
ዝተረፋ ኣለዋኒ ሕሹኽ ክብል ክነግራ።

ንኣኽን’የ ምሳኽን’የ ዝዛረብ ዘለኹ ስምዓኒ ከዋኽብቲ፡
ኣይረኣክናኣን ዲኽን ክትሓልፍ ብለይቲ፡
ሕይወት ዘለዋ ቆጽሊ’ያ ጽብቕቲ ለምለም ሰቲ።

* ብሰንኪ እርጋን ካሴት ኣነጺርና ክንሰምዖ ዘይከኣልና ቃላት

ካብ ዜማታት የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ)

ሕይወት ዘለዋ ቆጽሊ፡ ግን ድማ ትኸይድን . . . ትሳግምን፡ ዝገርም ኢዩ . . . እሞ ድማ ንየማነ 'ዚፈትዋ በአልቲ ቃልኪዳኑ' . . . ናብቲ ንሳ ዘላቶ 'ተሓቢሩ' ኪኸይድ ክቱር ድሌት ዘለዎ . . . ናበይ ከምዝኸደት ድማ ንከዋኽብቲ ብሓፈሻ ብፍላይ ንኾኸብ ጽባሕ ኣጥቢቁ ዚሓትት . . .ንጸልማት ኪጋልህ ኣብ ሃዋህው ዚሕምብስ . . . ምስ ወርሒ ኣማስዩ ምስ ከዋክብቲ ከዕልልን ኪሓትትን ዜውግሕ . . . ንፀሓይ ደሓን ሕደሪ ቢሉ ዚተሰናበተ . . . ጽባሕ ንግሆ ከምልማዳ ከምትበርቅ ፈሊጡ ኣሚኑ ብተስፋ ዚተጸበየ . . . ንስነፍጥረት ዘዘራረበ ኤርትራዊ ጥበበኛን ሓዋርያ ጥበብን . . . የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ ) ወትሩ ኣብ ልብና ይነብርን ይዝኸርን!

ለኢትዮጵያውያን ጥበብ አፍቃሪ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን እኛ ኤርትራውያን የመሃልና የመስመር ዳኞች የግጥሙን ግርድፍ ትርጉምና ይዘት እናስከትልላችኋለን . . . በኤርትራዊ ጭዋነት ኩራትና ትህትና ጭምር።
:mrgreen:
Last edited by Meleket on 05 Sep 2023, 10:28, edited 1 time in total.

Meleket
Member
Posts: 3057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ስነፍጥረትን ለማነጋገር የበቃ ኤርትራዊ የጥበብ ሰው - የማነ ገብረሚካኤል ባርያ - በስንኞቹ ሲዘከር

Post by Meleket » 30 Aug 2023, 11:03

ፀሓይ ደህና እደሪ፡

እስከ ነገ ጠዋት፡ ፀሓይ ደሕና እደሪ፡ ያኔ እስንክንገናኝ፡
ጨለማን ቀዝፌ፡ ፋና እያበራሁ፡ በሕዋ* ውስጥ ልዋኝ

በጨረቃ ኣምሽቸ፡ ላንጋ ከኽዋክብት፡
ደሕና እደሪ ፀሓይ፡ ነገ በማለዳ እስክትመጪ ጠዋት።

እናንተኑ እኮ ነው ስሙኝ ከዋኽብት፡
ኣላያችኋትም ወይ ስታልፍ በሌሊት፡
ያቺን ሕያው ተክል ለምለሚቱን በእውነት።

የማለዳው ኮከብ አንተ ኮከብ ጽባሕ፡
እንደምን አድረሃል እንደምነው ጤናህ፡
የፀሓይዋ መውጫ አንተው በማለዳ፡
ኣልሸኘሃትም ወይ ያቺን ሕያው ተክል ልትከፍልን ዕዳ።

ተነግሬ ልሂድ ዱካዋን ልከተል፡
ውዷ ባለቤቴን ያቺ ሕያው ተክል፡
እሄዳለሁ እኔ ባለችበት እሷ ፡
የልቤን ላዋያት ለራት ምሳ ቁርሷ።

እናንተኑ እኮ ነው ስሙኝ ከዋኽብት፡
ኣላያችኋትም ወይ ስታልፍ በሌሊት፡
ያቺን ሕያው ተክል ለምለሚቱን እውነት።

• ሕዋ እንጂ ውሃ ኣለመሆኑ ይጤን

ክየማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) ዜማዎች አንዱ
ሕያው የሆነች ተክል ግን ደግሞ ከቦታ ወደ ቦታ የምትንቀሳቀስ . . . የማነ እጅግ አድርጎ የሚያፈቅራት ባለቤቱ( ቃል ኪዳን የገባላት) . . . እሷ አለችበት ወደተባለው ተነግሮት ለመሄድ ብርቱ ፍላጐት የሞላው . . . ዬት እንደሄደችም ከዋክብትን አጥብቆ በመጠየቅ ከጨረቃ ጋር አምሽቶ ከከዋክብት ጋር ኣየተነጋገረና እየጠየቀ የሚያድር . . . ኮከብ ጽባህን አልሸኘሃትም ወይ በማለት በጥያቄ የሚወጥር . . . አስቀድሞ ፀሓይን እስከ ነገ ድረስ ደህና እደሪ በማለት . . . ነገ በማለዳ እንደ ልማዷ ጮራዋን እዬፈነጠቀች ዳግም እንደምትወጣ አጢኖ አምኖ በተስፋ የጠበቃት . . . ስነ ፍጥረትን ለማነጋገር የበቃ ጥበበኛና የጥበብ ሃዋርያ . . . የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) ሁሌም በልባችን ውስጥ የጥበብ ፏፏቴውን እያርከፈከፍብን በጥበባዊ ምዑዝ ሽታው እያወደን ለዘለዓለሙ እዬተዘከረ ይኖራል።

DefendTheTruth
Member+
Posts: 9949
Joined: 08 Mar 2014, 16:32

Re: ስነፍጥረትን ለማነጋገር የበቃ ኤርትራዊ የጥበብ ሰው - የማነ ገብረሚካኤል ባርያ - በስንኞቹ ሲዘከር

Post by DefendTheTruth » 30 Aug 2023, 11:32

እናመሰግናለን፣ መለከት፣

ጓደኞች ነበሩኝ፣ ይህን ስም በጣም የምወዱ፣ እኔ ትግርኛን ስለማልችል የሱን ሙዚቃዎች ብዙም አላጣጠምኩኝም። ግጥሙ ደስ ይላል።

እስኪ እንግዲህ በነካ እጅህ/እጅሽ የግጥሙን ሙዚቃም በዛዉ ጀባ በለን/በይን፣ እናመሰግናለን፤ በቅድሚያ!

Tog Wajale E.R.
Member+
Posts: 9986
Joined: 31 Oct 2019, 15:07

Re: ስነፍጥረትን ለማነጋገር የበቃ ኤርትራዊ የጥበብ ሰው - የማነ ገብረሚካኤል ባርያ - በስንኞቹ ሲዘከር

Post by Tog Wajale E.R. » 30 Aug 2023, 11:58

ክልተ፥ ዕስቱኻት፥ ዓጋመ፥ ወይለኹም !!

ጎይቶትኩም፥ ሻዕቢያ፥ ምስ፥ ጀጋኑ፥ ፋኖ !!
ንመጻኩም፥ ኣለና !!

Meleket
Member
Posts: 3057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ስነፍጥረትን ለማነጋገር የበቃ ኤርትራዊ የጥበብ ሰው - የማነ ገብረሚካኤል ባርያ - በስንኞቹ ሲዘከር

Post by Meleket » 02 Sep 2023, 11:08

ወዳጃችን DefendTheTruth ለግዜው እላይ ግጥሙን የጻፍነው ዜማን በብይነመረቡ ውስጥ ጐልጉለን ልናገኘው ኣልቻልንም። ይህኛው የየማነ ገብረሚካኤል ዜማ፡ ከቀደምት ዜማዎቹ ኣንዱ ሳይሆን እንደማይቀር እንገምታለን። ብቻውን በጊታር ወይም በዑድ በተባለ የሙዚቃ መሳርያ ዬተጫወተው ዜማ ነው፡ ልዩ የቁጭት እንጉርጉሮም ይታይበታል። ታዋቂው ኤርትራዊ አንጋፋ የጥበብ ሰው በረኸት መንግስተአብ እንዲህ ዓይነቶቹን ዬዬማነን ዜማዎች "ሰቆቃዎ-ኤርትራ" የሚታይበት "ሰቆቃው-የማነ" በማለት ሁነኛ ስምን ሰጥቷቸዋል። ይህ ሲባል ግን የማነ ሌሎችም የተለያዩ የዜማ ስልቶችንም እጅግ በሚያምር መልኩ አንጎራጉሯል። እስቲ ቀስ በቀስ አንዳንዶቹን የግጥሙን ይዘቶች ለማጋራት እንሞክራለን። ሁነኛ ኤርትራውያን ካሉ ደግሞ ዜማዎቹን ከጐልጉሉ ፈትሸው ያጋሩናል።

እኒያ የማነን በጣም የሚወዱት ጓደኞችህስ ደህና ናቸው ወይ? እስቲ እነሱንም ጠይቃቸው ዜማቹን እንዲያጋሩን። እነ ዘባራቂው Tog Wajale E.R. እንደሆኑ ኤርትራዊ ታሪክ በየመድረኩ ሲነገር ሲሰሙ ያጥወለውላቸዋል። አንድም ቀን ኤርትራዊ ታሪክን ለህዝብ ሲገልጡም ኣላዬንም። በዬሄዱበት መዝረክረክና በያጥሩ መጸዳዳት እንጂ፡ ስለ ጥበብና የጥበብ ሰዎች ሚና ለመወያዬት ምንም ዓይነት ብቃት ዬላቸውም።

DefendTheTruth wrote:
30 Aug 2023, 11:32
እናመሰግናለን፣ መለከት፣

ጓደኞች ነበሩኝ፣ ይህን ስም በጣም የምወዱ፣ እኔ ትግርኛን ስለማልችል የሱን ሙዚቃዎች ብዙም አላጣጠምኩኝም። ግጥሙ ደስ ይላል።

እስኪ እንግዲህ በነካ እጅህ/እጅሽ የግጥሙን ሙዚቃም በዛዉ ጀባ በለን/በይን፣ እናመሰግናለን፤ በቅድሚያ!
Tog Wajale E.R. wrote:
30 Aug 2023, 11:58
. . .
በነገራችን ላይ ይህችኛይቱ የየማነ ዜማ፡ ለኤርትራ ባንዴራ ያዜማት ነው ዬሚመስለው። ፌዴሬሽን ፈርሶ፡ የኤርትራ ባንዴራ ከቦታዋ ተነስታ የነ Tog Wajale E.R.ባንዴራ መውለብለብ ስትጀምር፡ የቅጠል ምስል ያለባት የኤርትራዋ ባንዴራ ደግሞ በረሃ ለበረሃ ስትንከራተት፡ የማነ ቁጭት ተሰምቶት ለሷ ያንጐራጐረላት ይመስላል። በዚህና በመሰል ዜማዎቹ የያኔዎቹን ወጣቶች ወደ ትግሉ እንዲሰማሩ ጉልህ ሚና መጫወቱን ብዙዎች ይስማሙበታል።

ከቦታ ቦታ የምትንቀሳቀስ ህያው ተክል . . . የኤርትራ ባንዴራ
:mrgreen:

Meleket
Member
Posts: 3057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ስነፍጥረትን ለማነጋገር የበቃ ኤርትራዊ የጥበብ ሰው - የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) - በስንኞቹ ሲዘከር

Post by Meleket » 05 Sep 2023, 10:25

ድጕዓ የማነ . . . ድጕዓ ኤርትራ . . . ሰቆቃ የማነ . . . ሰቆቃ ኤርትራ
ሉላ

ምሳይ ዝነበረት ብፍቕሪ ሓቢራ፡
ሓደ ወሲዱለይ ረኺበ መከራ።
ብሓይሊ ዘሪፍዋ ጭፍርኡ ሰዲዱ፡
ምሳይ ዝነበረት ወሲዱዋ ዓዱ።

እንታዋይ ደፋር’ዩ መን’ዩ ዘሕደገኒ፡
ክንደይከ ይጭክን ዓይነይ ዘንቈረኒ።

ብሃንደበት ከይዳ ዘሊላ፡
አይፈለጥኩን ኣበይ ከምዘላ፡
ወሲዶምለይ ኣሕዲጎምኒ ዘሪፎማ ሉላ።

ደሃያ ሳኢነ ዘላቶ ጠፊኡኒ፡
ደልየ ስኢነያ ሰለሎ አትዩኒ።
ኣደ ስድራ ነይራ በዓልቲ ቃልኪዳነይ፡
ተፈላሊና ግን ዘኽታማት ኮይኖም ደቀይ።
በጃኹም ድለይዋ ደቃ ከተዕቢ፡
ሓላዊ ዘይብሎም ከይነኽሶም ከልቢ።

ብሃንደበት ከይዳ ዘሊላ፡
አይነገረትንን ኣበይ ከምዘላ፡
ወሲዶማ እምበር አሕዲጎምኒ እምበር ዘሪፎ’ማ ሉላ።

ብሓዘን ተዋሒጦም ደቀይ ብናፍቖታ፡
ገፊሕ ንእዲ ገዲፎም ደቂሶም ኣብ ባይታ።
ብሓዘን ተዋሒጦም ደቀይ ብናፍቖታ፡
ገፊሕ ዓራት ገዲፎም ደቂሶም ኣብ ባይታ።


ሉላ እናበሉ ሽማ ክጽዉዑ፡
ነዲኦም ስኢኖም ዘኽታማት ቆልዑ።
ከየቕንእዎም መታን ቖልዑ ጎረባብቲ፡
ንሉላ ጸውዑሎም ናይ ገዛ መብራህቲ።

ብሃንደበት ከይዳ ዘሊላ፡
አይፈለጥኩን ኣበይ ከምዘላ፡
ወሲዶምለይ ኣሕዲጎምኒ ዘሪፎማ ሉላ።

ደቀይ ኣንጸርጺሮም ኣብ ዘይውደቕ ከይወድቁ፡
ኣሕዋት ሓግዙኒ ካብ ኢደይ ከይመልቝ።
በይና ከይትተርፍ ንእሽቶ ገዛና፡
ጸላኢ ከይሕጎስ ወራሲ ዘይብልና።
ሻማ ከይብሉዎ ከይጻወትሉ፡
ንሉላ ጸውዑለይ ገዛና ክትሕሉ።


ኣብዚ “ሰቆቃዊ” መበቆላዊ ዜማ ‘ሉላ’፡ ባርያ ከምዚ ኢሉ ብምድጓዕ ይፍልም
ሉላ ጠፊኣትኒ፡ ዝረኣያ ዓይኑ ይብራህ
በጃኹም ንገሩኒ፡ ልብኹም ኣይፍራሕ።
ዋይ ኣነ
ሉላ ምበር ኣጥፊኤያ፡
ኣይኑ ይብራህ ዝረኣያ።
ሉላ ሉላ
ፍቕርኺ፡ ኣብ ልበይ ሰፈራ!

ብምባል እናስተንተነን እናጐሃየን የስቆርቁር። ኣብቲ ብዘመናዊ መልክዕ ዝደረፎ ዜማ፡ እዚ ብጊታር ዝተጻወቶ ግጥምታት ገሊኡ ጐዲሉን ተመሓይሹን ኢዩ ቀሪቡ። ግሩም ምስትምቓር! ሉላ ግን መን ኢያ? :mrgreen:

መፍቀርቲ የማነ ንዜማታቱ ከተካፍሉና ብኽብሪ ዓዲምናኹም ኣሎና!

Meleket
Member
Posts: 3057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: Re: ስነፍጥረትን ለማነጋገር የበቃ ኤርትራዊ የጥበብ ሰው - የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) - በስንኞቹ ሲዘከር

Post by Meleket » 06 Sep 2023, 09:36

ኤርትራዊው ጥቁር አልማዝ ፡ የማነ ገብረሚካኤል ብስራት፡ ባርያ በሚል ቅጽል ስም ሲጠራ፤ ለብዙዎች ችግረኞች ኣባት በመሆኑና፡ ያለውን ሃብት በሙሉ ለድሆች በማካፈሉ፡ በኤርትራውያን ልብ ውስጥ የርህራሄ ተምሳሌት በመሆኑ "የድሆች ኣባት" ተብሎም በሰፊው ይታወቃል።



ኣባቱ ግራዝማች ገብረሚካኤል ብስራት የታወቁ ጋዜጠኛ ሲሆኑ “ዘመን” ተብሎ ለሚታወቀው ኤርትራዊ ጋዜጣ አዘጋጅ ሆነው አገልግለዋል። እናቱ ወይዘሮ ኣዜብ ገብረህይወት ይባላሉ። የተወለደውም ኣሥመራ እምብርት ውስጥ ኣባሻውል በተባለ ስፍራ በጃንዋሪ 21 1949 እ.ኤ.ኣ ሲሆን ያረፈውም ኣሥመራ ውስጥ በ1997 እ.ኤ.ኣ ነው። የመጀመርያ ደረጃ እና መለስተኛ ደረጃ ትምህርቱን በኪዳነምሕረት እና በዳንኤል ኮምቦኒ ትምህርት ቤቶች ሲከታተል ቆይቶ በኋላም በቅድስት ማርያም ትምህርት ቤትም ለ3 ወራት መማሩን መዛግብት ይመሰክራሉ። በጠባዩ እጅግ ምስጉንና ጭምት ለጋሽና ርኅሩህ፤ በትምህርቱ ደግሞ እጅግ ንቁና ፈጣን ኣእምሮ ካላቸው ጋር የሚመደብ ኣስተዋይ ተማሪ እንደነበርም ብዙዎች የኮምቦኒ ትምህርት ቤት አብሮአደጎቹና 'ስካውት' ጓዶቹ ይገልጻሉ።

የስነጥበብ ፍቅር ከአካዳሚያዊ ትምህርት ይበልጥ በልቡ ውስጥ ስላደረና ስላገረሸበት፤ ምንም እንኳ የወላጅ አባቱ ፍላጐት በአካዳሚው እንዲገፋ ቢሆንም ቅሉ፡ የልቡ መሻት ወደ ኪነጥበቡ ስላደላ፤ በዚሁ ሙያው ልዩ ተሰጥዖው ከግዜ ወደ ግዜ እየገነፈለና እየጎላ በመሄዱ፡ በዚሁ የስነጥበብ ዓለም መዋኘቱን የህይወቱ ጥሪ አድርጎ ተቀብሏል። አባቱም ጭምር የነበሩበትን የሳንሱር ክፍል እግድ ሳይቀር በመተላለፍ፡ ምርጥ በሆኑ ግጥሞቹና ዜማዎቹ ለኤርትራ ህዝብ የነጻነት ትግል ቀስቃሽ እንጉርጉሮችን በማንጎራጐሩ፡ በዚህች "ሉላ" በተሰኘችው ሙዚቃው ምክንያትም ጭምር ወህኒቤት ድረስ ተወርውሮ ነበር። ዳግም ‘ሉላን’ እንዳይዘፍን ማዕቀብ ተደርጎበት ከእስር ቢወጣም፡ ሉላ ግን በዘመኑ ወጣቶች ልብ ውስጥ በመቀረጿ ኣላፊ ኣግዳሚው ሳይቀር ዬሚያንጎራጉራት የትግል ቀስቃሽ ዜማ ለመሆን በቅታ ነበር።

ኤርትራዊው ጥቁር ኮከብ ተብሎም የሚታወቀው ባርያ የሙዚቃና የተውኔት የግጥምና የዜማ ክህሎቱን በሚገባ ለህዝብ ካስተዋወቀ በኋላ፡ እንዳሻው ማዜምና መግጠም እንዳይችል ክትትል ሲበዛበትም፡ ከስነጥበብ ትግሉ በተጨማሪ በአካልም ወደ ነጻነት ትግሉ እንደተቀላቀለም ይታወቃል፡ ባርያ ‘የህዝቡ-ባርያና ኣገልጋይ’ የማነ ገብረሚካኤል ብስራት!

ለዛሬ ይህችን ‘ሉላ’ የተሰኘች የየማነ (ባርያ) ምርጥ ዜማ፡ የግጥም ስንኞችን 'ግርድፍ ትርጉም' እንኮምኩም እስቲ!
https://sonichits.com/video/Yemane_Bary ... 1#page-tab

ሉላ

ከኔጋ የነበረች የፍቅር እመቤቴን፡
አንዱ ወሰደብኝ ኣያሳየኝ ፍዳዬን።
ጭፍራውን በመላክ በኃይሉ ቀምቶ፡
ሃገሩ ወሰዳት፡ ከመዳፌ አውጥቶ።
ምንኛ ደፋር ነው ምንኛ አረመኔ፡
ጨክኖ አንቆረኝ ብርሃኒቱን የዓይኔ።


በድንገት ከንፋ ነው፡ በራ የሄደች፡
በምኔ ልወቀው ወዴት እንደገባች፡
ሉላን ወሰዱብኝ ሉላን ዘረፉብኝ እኒያ ቀማኞች።

የት ይሆን ያለችው፡ ያለችበት ጠፋኝ፡
ፈላልጌ ኣጣኋት፡ እጅግ በጣም ከፋኝ።
የልጆቸ ምርጥ-እናት፡ ውዷ ባለቤቴ፡
እናት-ኣልባ ሆኑ፡ ኣንቺን በማጣቴ።

እባካችሁ ፈልጓት ልጆቻችንን ታሳድግ፡
ውሻ እንዳይነክሳቸው፡ አጥትው መከታ ጥግ።

በድንገት ከንፋ ነው፡ በራ የሄደች፡
በምኔ ልወቀው ወዴት እንደገባች፡
ሉላን ወሰዱብኝ ሉላን ዘረፉብኝ እኒያ ቀማኞች፡
ፈላልጌ ኣጣኋት የት ይሆን የገባች።

ልጆቻችን ናፍቀዋት በሃዘን ማቀቁ፡
ሰፊውን መደብ ትተው፡ መሬት ላይ ወደቁ።
ልጆቻችን ተከፍተው በሃዘን ደቀቁ፡
ሰፊውን አልጋ ትተው፡ መሬት ላይ ወደቁ።

እናት ዓለም ሉላ ብለው እየጠሩ፡
ባላባት ብቻ ሆነው፡ እናት-አልባ ቀሩ።
የጐረቤት ልጆች እንዳያስቀኗቸው፡
የቤታችንን መብራት ሉላን ጥሩላቸው።

በድንገት ከንፋ ነው በራ የሄደች፡
በምኔ ልወቀው ወዴት እንደገባች፡
ሉላን ወሰዱብኝ ሉላን ዘረፉብኝ እኒያ ቀማኞች፡
ፈላልጌ ኣጣኋት የት ይሆን የገባች።

ልጆቻችን ከፍቷቸው እንዳይሳነፉ፡
ዘመድ ኣዝማድ እርዱኝ ከእጄ እናዳይጠፉ።

ትንሿ ቤታችን ብቻዋን እንዳትቀር፡
ጠላት እንዳይደሰት፡ ሲጠፋ የኛ ዘር።

እንዳይጫወቱበት የቤታችንን ሃብት፡
ሉላን ጥሯትና ትታደግ የኛን ቤት።
እንዳይቀራመቱት የቤታችንን ሃብት፡
ሉላን ጥሯትና ትውረሰው የኛን ቤት።




የማነ ገብረሚካኤል “ሰቆቃዊ” በሆነ አቀራረብ፡ በወቅቱ የነበረውን የፖለቲካ ሁኔታ በሚያንጸባርቅ መልኩ፡ ስለ ሉላ በጊታር ያንጐራጐረውን፤ ቆይቶ በዘመናዊ መሳርያዎች ታጅቦ ዳግም ኣንጐራጉሮታል። ታዋቂው ኤርትራዊ አንጋፋ የጥበብ ሰው በረኸት መንግስተኣብ “የማነ ይበልጥ በደልንና የህዝብ ጭቆናን ነው ፍንትው አድርጎ በጥበቡ የሚያንጸባርቀው” በማለት ለጥበብ ኣጋሩ ለየማነ ምስክርነቱን እንደሰጠም ይታወቃል።

ይህቺ ሉላ እያለ ያንጐራጐረላት ባለቤቱ ደግሞ ኤርትራ መሆኗ በብዙዎች ዘንድ ይታወቃል። ይህ ኤርትራዊ ጥቁር ኣልማዝ በብዙዎች የጥበብ ኣፍቃሪዎች ልብ ውስጥ ሁሌም ህያው ሆኖ በክብር ዙፋን ተቀምጦ ይኖራል።

Meleket
Member
Posts: 3057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: Re: ስነፍጥረትን ለማነጋገር የበቃ ኤርትራዊ የጥበብ ሰው - የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) - በስንኞቹ ሲዘከር

Post by Meleket » 09 Sep 2023, 03:06

የማነ ፈቓር ኢዩ፡ ንፍቅሪ’ከ ብከመይ ጥበብ ገሊጽዎ’ሎ እስከ ነዚኣ “ንዓኺ ዝሃበ ንመን ሂቡ ግርማ” እትብል ግጥሙ ነስተማቕራ።

ስኒትን ውህደትን፡ ግጥሚን ዜማን፡ የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) ካብቶም ዕጹብ ድንቂ ዚበሃሉ ገለጽቲ ስምረት ሃሳብን ዜማን ከምዝኾኑ፡ አስተማቐርቲ ጥበብ ጥራሕ ዘይኰኑስ፡ ‘ጸላእቲ-ጥበብ እዉን እንተልዮም’ ከይፈተው ከድንቝዎ ይግደዱ ኢዮም። ግደ ሓቂ ንየማነ ገብረሚካኤል ኣብ ነፍስ ወከፍ ደርፍታቱ ዘሰነይዎ ሙዚቀይናታት’ውን ብሓፈሻ ዓቢ ክብሪ ኪወሃቡ ይግባእ፤ እቲ ምንታይ ብመንፈስን ብኣካልን ብዕላማን እንተዘይወሃሃዱ ነቢሮም፡ ነዚ ኣፍርዮሞ ዘለዉ መሳጢ ዜማታት ክንሰምዕ ኣይምከኣልናን ኔርና፡ ኣብነት ውህደትን ኣብነት ስኒትን ክንዲዝኾኑ ነመስግኖም ኣሎና፡ ብኤርትራዊ ጭዉነትን ሓበንን።

እስከ ንሎሚ መስከረምን ሓዲሽ ዓመት ግእዝን ካብ መጹና - ብዛዕባ ፍቕሪ - ዕምባባ መስከረም ጽቡቕ ደርጊስኒ - እናበለ ኣብታ “ንዓኺ ዝሃበ ንመን ሂቡ ግርማ” እትብል ግጥሙን ዜማኡ ዝሰዅዐን ቃላት ነስተማቕር። “ትግርኛ ገላጺ ኣይዀነን፡ ንፍቕሪ ብትግርኛ ኣይትገልጾን ኢኻ” ዚብሉ ሰንኮፍ ሃሳብ ዘለዎም ሰባት፡ ብርግጽ ፍቕርን ምልከትን ትግርኛ ዘይብሎምን፡ ንዜማታት ዬማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) ፈጺሞም ሰሚዖም ዘይፈልጡ ኺኾኑ ኣለዎም። ነዚ ክቡር ህያብ ንህዝቢ ኤርትራ ንዘበርከቱ ብፍላይ ንግራዝማች ገብረሚካኤል ብስራትን ወይዘሮ ኣዜብ ገብረህይወትን ስድራቤት የማነን ( በዓልቲ ቤቱን ደቁን ኣሕዋቱን ኣሓቱን) ከምኡዉን ንኩሎም መምህራኑ ብሓፈሻ ልዑል ኣኽብሮትን ምስጋናን ኣሎና፡ አስተማቐርቲ ጥበብ ንሕና ኤርትራዉያን ደያኑ ማእከልን መስመርን።

ንዓኺ ዝሃበ ንመን ሂቡ ግርማ

ንዓኺ ዝሃበ ንመን ሂቡ ግርማ፡
ስጉምቲ ኣካይዳ ኣከዳድና፡
ልቦና ህያውነት እሩም ጠባይ፡
ቁንጅና መልክዕ ቅርጺ ኣፈላላይ፡
መግለጺ ኣይርከቦን መልክዓ፡
ኣብ ጸልማት ተብርህ ተወሊዓ።

ስሩዕ ኣካላታ ኣታክልቲ ወይኒ፡
ዕምባባ መስከረም ጽቡቕ ደርጊስኒ፡
ተፈትኡ ኩሕል ፈናጅል ዓዒንታ፡
ጸጉሪ ርእሳ ሃሪ ስገም ኣፃብዕታ።

ደመና ቀዲዳ እትወጽዕ ፀሓይ፡
ብማዕዶ ትልለ ድሙቕ ኾኸብ ሰማይ።

ዉህልነትን ጽፈትን ንናብራ ሓዳር፡
ኢንታ ዘይወጻ ወለላ መዓር፡
ፈታጊት፡ ፈታሊት ጥልፊ ቅጭን ኩታ፡
ቅሔ ጽልሚ ስፈ መሶብ ጥልፍታታ።

ሕማቅ ዘይወጻ ጥዕምቲ መዓዛ፡
ሓብሓቢት ስድራቤት ዓንዲ ማእከል ገዛ።

ዘይትነጽፍ ቀላይ ፈልፋሊት ዒላ ፍቕሪ፡
ወትሩ እትሕጎስ ምንም ዘይትኹሪ፡
ፈታዊት ሓዳራ ከም ነብሳ ትሓሊ፡
ሕያወይቲ ርግቢት ንደቓ ትዓሊ።


ኣብ ጎረቤትና ያኢ፡ ሓደ ‘ቀርሳኒ-ዜማ’ ንዜማ የማነ ባርያ ጨዉዩ፡ የማነ ንኣፍቓሪቱ ንዝደረፎ ደርፊ፡ እዚ ወዲ ጐረቤትና ነዚ መስተንክራዊ ግጥሚ የማነ ጐስዩ፡ ንመርካቶ ናይ ኣዲስ ኣበባ (ኣደይ ንስኺ ኢኺ፡ ብዘይካኺ አደ ዬብለይን) እናበለ ኪቖጻጸ ርኢናዮ። ብዘይ ጠስምካ ወለል ብዘይ ዝርያኻ ሰለል . . . . እዚ ወዲ ጐረቤትና ከይተፈለጦ ዝመስከሮ ሓቂ፡ ብዜማ ንፍቕሪ ኣብ ምግላጽ፡ እዚኣ ዜማ የማነ መዳርግቲ ኣልቦ ከምዝዀነት ኢዩ። ግደ ሓቂ የማነ ንዝደረሳስ ፍቕራዊ ግጥሚ እዛ ዜማ እዚ ወዲ ጐረቤትና እንተዘስተማቕራ ነቢሩ፡ 'መርካቶ' እናበለ ኣይምተለለዎን።

ኣቐዲምና ዘስተማቐርናያ ዜማ፡ የማነ “ሉላ ጠፊኣትኒ’ ቢሉ ከምዝዘየመ ንዝኽር፡ ድሒሩ ‘ሉላ ረኺበያ” ቢሉ፡ ሉላ ደብዳቤ ከምዝሰደደትሉ’ሞ ኣብ ማኅዩር ተሞቂሓ ከምዘላ፡ ምስ ኩሎም ፈተውቱ ሰሚሩ ድማ ካብ ማኅዩር ሓራ ኪገብራ ከምዘለዎ ዜስምዕ ካልኣይቲ ዜማ’ውን ኣዚሙ ኢዩ። የማነ ንደርፍታቱ ከይተረፈ ብሰንሰለታዊ ዛንታ ከተኣሳስር ዝከኣለ ግሩም ደራሲዉን ኢዩ ኔሩ።

“ኤርትራና ብዙሓት የማነታት ኣፍርያ ኢያ፡ ኣደ ብዙሓት የማነታት’ውን ኢያ፤ መሳጢ ግሩም ግጥሚን ዜማን ኣብ ምፍልፋል፡ ንሓፋሽ ንሃገራዊ ናጽነት ኣብምብርባር፡ ኣብ ልግሲ፡ ኣብ ህያውነት፡ ጎር ድኻታት ኣብ ምዃን፡ ኣብ ልቢ ሓፋሽ ክቡር ቦታ ኣብ ምሓዝ፡ መን ከም የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ)!” እንተተባህለ መን ሓሶት ክብል ይኽእል? . . . ሰማእታት ኤርትራ ወትሩ ይኽበሩ!

Meleket
Member
Posts: 3057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: Re: ስነፍጥረትን ለማነጋገር የበቃ ኤርትራዊ የጥበብ ሰው - የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) - በስንኞቹ ሲዘከር

Post by Meleket » 09 Sep 2023, 04:09

የማነ ፍቅርን በግጥም ብቻ ሳይሆን በዜማ ለመግለጽ የበቃ የጥበብ አልማዝ ነው።

የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) የትግርኛ የስነጽሑፍ ብስለቱን በማጎልበት ረገድ የወላጆቹና የመምህራኖቹ ሚና ከፍተኛ እንደነበር፡ ከግጥሞቹ መገንዘብ ይቻላል። ብዙዎች ትግርኛ ቋንቋ ፍቅርን ኣይገልጥም በማለት ለማንቋንሸሽ በሚፍጨረጨሩበት ወቅት የማነ ህዝብን ለሃገራዊ ነጻነት ከማነቃቃት በተጨማሪ የህዝቡን ባህላዊ ትንሳኤ በማወጅ ረገድ ውብ በሆኑት የትግርኛ ስነግጥሞቹና ዜማዎቹም ጉልህ ስራ ሰርቷል። የየማነ የፍቅር ዜማዎች እጅግ የረቀቁ ከመሆናቸው የተነሳ ከዜማዎቹ ኣንዷ በመርካቶና አዲስ አበባ ፍቅር በተሰለበ አንድ ድምጻዊ ስትዜም ሰምተናል።

ለምሳሌ ይህ በመርካቶና በአዲስ አበባ ፍቅር የተነደፈ ወጣት፡ ለመርካቶና ለአዲስአባባ ያለውን ፍቕር ለመግለጽ፡ ከእልፍ አእላፍ ኢትዮጵያዊ የፍቅር ዜማዎች ይልቅ፡ የየማነን የፍቅር ዜማ ነው ለመጠቀም የመረጠው። ይህ ኢትዮጵያዊ “ያለ አዲስ አበባና ያለ መርካቶ ሌላ እናት የለኝም” እያለ ያንጎራጐረው ወጣት፡ የየማነን ዜማ ግጥም ለማጣጣም ቢሞክር ኖሮ፡ በርግጥ መርካቶን ለማዳነቅ መጋጋጥ ባላስፈለገው ነበር፡ ይልቅስ የየማነን የፍቅር ዜማ፡ ከየማነ የፍቅር ግጥም ጋር በማቀናጀት ባንጎራጎረና በያንዳንዱ ኣፍቃሪ ልብ ውስጥ ለዘለዓለም መኖር በቻለ ነበር።

እርግጥ ነው የማነም የሙዚቃ ህይወቱን በጀመረበት ወቅት የዑስማን አብደረሒምን “ፍቕሪ ዕውር ዓሚነ ተሳቀኩ ወይ ኣነ ድቃስ እኳ ስኢነ” የሚለውን “ዕዉሩን ፍቅር አምኜ፡ ተሰቃየሁ፡ እንቅልፍ ባይኔ ኣልዞር ኣለኝ” የሚለውን ምርጥ ዜማ አዚሞ ስለተነሳ፡ የሱን ዜማ ሌሎች ሲያዜሙት ቅያሜ አይኖረውም። እኒህ ኣዚያሚዎች ግን የግጥሙን ውበትም እንዲረዱለት ሳይሻ ኣይቀርም ብለን እንገምታለን።

የትክክለኛው የየማነ ዜማ ግጥም ይዞታው ግን ፍቅራዊና ይህን የሚመስል ነው። የማነ ፍቅርን በደንብ አድርገው ከገለጡ ጉምቱ ኤርትራውያን የጥበብ ሰዎች አንዱና ዋነኛው ነው። እስቲ ለዛሬ የየማነን ፍቅራዊ ግጥም “ግርድፍ ትርጉም” ከትንሽ ቅመም ጋር ቀላቅለን እናጣጥም።

https://www.youtube.com/watch?v=2esPYC_cEyw

እንዳንቺ ግርማ ሞገስ፡ ኣምላኽ ለማን ሰጥቶ

እንዳንቺ ግርማ ሞገስ፡ ኣምላኽ ለማን ሰጥቶ፡
አካሄድ አለባበስሽ፡ መቶ ነው ከመቶ።

ጠባይዋ ወርቃማ ልቦናዋ ያማረ፡
ቁንጅናና መልኳ ቅርጿ የሰመረ።
መግለጫ’ማ ዬለም ልዩ ነው ውበቷ፡
የጨለማ ፋና ደማቅ ነው ፍካቷ።

ቁመና ኣካላቷ የወይን ተክል፡
ጥርሷ ያደይ-ኣበባ እጅግ ሚያማልል፡
በኩል የታጀቡ ኣይኖቿ ፍንጃል፡
የራስ ጸጉሯ ሃር፡ ጣቶቿ ምልምል።

ደመናን ሰንጥቃ እንደወጣች ጸሓይ፡
ከሩቅ ስታበራ ደምቃ የምትታይ።

ጥበብ ባልትናዋ ምቹ ለትዳር፡
እንከንየለሽ ቆንጆ ወለላ ናት ማር።
እህልን ፈታጊ፡ ፈታይ ለነጠላ፡
ለጋቢና ኩታ ለጥልፍ በጠቅላላ።
ሰፌድና መሶብ ስትሰፋ ላያት፡
ብሎ ይጠይቃል “በርግጥ ይቺ ሰው ናት?” :mrgreen:

ክፉ ኣይወጣም ካፏ፡ መዓዛዋ ጣፋጭ፡
ምሰሶ ለቤቷ፡ ርህራሄን ገላጭ።

የፍቅር ባህር ነች፡ ምንጯ የማይነጥፍ፡
ሁሌ ደስተኛ ጭራሽ ማታውቅ ማኩረፍ።

እንደ ራሷ አድርጋ ትዳሯን ኣክባሪ፡
ልጆቿን ሰብሳቢ በፍቅር ጠማሪ፡
ሰው ናት ወይስ መልኣኽ እንደ እርግብ በራሪ።
:mrgreen:

በነገራችን ላይ ባለፈው ግጥም ላይ ያየናት “ሉላ ጠፋችብኝ” ብሎ የተከዘው የማነ፡ በቀጣዩ ዜማው “ሉላ ተገኝታለች” ብሎ በማንጉራጎር፡ ለህዝብ ተስፋ ሰጥቷል። “ሉላ ተገኝታለች” በምትለው ዜማው፡ ሉላ ባልታወቁ ስዎች አማካኝነት ደብዳቤ እንደጻፈችለትና፡ በሰንሰለት ተጠፍራ እስር ቤት ውስጥ እንደገባች፡ ከጓዶቹ ጋር በመሆን ከእስር እንድትፈታ እንደተማጸነችው በሚገልጽ መልኩ አዚሟል። የማነ ዘፈኖቹን በመቀጣጠል ረዚም ትረኻም መተረኽ የሚችል ደራሲም ነበር።

መልካም አዲስ ግዕዝዊ ዓመተምሕረት ለመላው የዚህ መድረክ ተሳታፊ እዬተመኘን ከየማነ ባርያ የሙዚቃና ግጥም ስራዎች አልፎ አልፎ ለመጋራት እንሞክራለን። መልካም መልካሙን ሁሉ ተመኘንላችሁ፡ እኛ ኤርትራውያን የመሃልና የመስመር ዳኞች፡ በኤርትራዊ ጭዋነት ኩራትና ትህትና ጭምር።

Meleket
Member
Posts: 3057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: Re: ስነፍጥረትን ለማነጋገር የበቃ ኤርትራዊ የጥበብ ሰው - የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) - በስንኞቹ ሲዘከር

Post by Meleket » 15 Sep 2023, 05:07

የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) በቲ ክቡር ስነጥበባዊ ላዛኡ፡ ምስ ስነ ፍጥረት’ውን ኪዘራረብ በቒዑ ክንብል ከሎና፡ ምስ ከዋክብቲን ወርሕን ጸሓይን ስለዝዕለለ ጥራሕ ኣይኰነን፤ እንታይ ደኣ ምስ ወደባት ዓድና’ውን በታ “ወደባት ዓደይ” ትብል ደርፉ ኔሩ ስለዘዕለለ’ውን ኢዩ። የማነ አብ ግጥሙን ዜማኡን፡ “ወደባት ዓደይ ይረኣየኒ’ሎ” ጥራሕ ኣይኰነን ዝበለ፤ እንታይ ደኣ “ወደባት ዓደይ የዛርበኒ’ሎ!” . . . . "የዛርበኒ’ሎ!" ብርግጽ ወደባት ዓዱ የዛርቦን የዘራርቦን፡ ነቲ ፍትው ስነጥበባዊ የማነ ባርያ። ጉዳይ ወደባቱ'ውን የዛርቦ፡ ንባርያ ሕዝቡ!

ጌጋ ይኽልኣልና እምበር፡ የማነ ነዚን ከምዚን ዝኣመሰለ ንሓፋሽ ብወኒ ንቃልሲ ዘበራብር ዜማ ሳላ ዘዘዬመ፡ ኣብ ድባርዋን ከባቢኣን ንዝነበረ ማዕድናዊ ትሕዝቶ ኤርትራ ንምምዝማዝ ዝነጥፉ ንዝነበሩ ኢትዮኒቦን ዚበሃሉ ትካል፡ ብሓርበይናታት ኤርትራውያን ተጋደልቲ ጀብሃ መጥቃዕቲ ተፈንይዎም፡ ነቲ መዝማዚ ስርሖምን ሓፋሽ ኤርትራዊ ዘይርብሓሉ ተግባር ንከቋርጹ ከምዝተገደዱ ንግምት። እስከ እቶም ትፈልጡ ብፍላይ ሰብ ድባርዋ ሓብሩና “እዛ ዜማ የማነ’ዶ” ትቕድም ወላስ “መጥቃዕቲ ተጋደልቲ ጀብሃ ኣብ ቦታ ዕደና ዱባርዋ” . . .

ሕጂ ናብ ምስትምቃር ግጥምታት ናይዛ ወርቃዊት ዜማኡ . . . ወደባት ዓደይ

ወደባት ዓደይ

ላለይ ላሎ፡/2/
ወደባት ዓደይ የዛርበኒ’ሎ።
ንዑናይ ምሳይ በቲ ኣንጎሎ፡
ወደባት ዓደይ ይረኣየኒ’ሎ።

በስመኣብ ኢለ ክጭርስ ደርፈይ፡
ናባኹም ክሰዶ ቆላሕታ ኣዒንተይ፡
ወደባት ኢለ ክዓጹ ደርፈይ፡
ናባክን ክሰዶ ቆላሕታ ኣዒንተይ፡
. . . . . . ወደባት ናይ ዓደይ።

ላለይ ላሎ/2/፡
ወደባት ዓደይ የዛርበኒ’ሎ።

ምጽዋዕ ዓሰብ ኣዱሊስ ዙላ፡
ደሴታት ዳህላክ ምስ ደሴታት ናኹራ፡
ሰላም ኣብዚ ኮይነ ናይ ናፍቆት ማሕላ።

ላለይ ላሎ/2/፡
ወደባት ዓደይ የዛርበኒ’ሎ
ንዕናይ ምሳይ ኣንቲ ወለሎ፡
ወደባት ዓደይ የዛርበኒ’ሎ

ሰዓት ኣኺሉ መርከብ ነቒላ፡
ካብ ምጽዋዕ ዓሰብ ብኣዱሊስ ዙላ፡
ሰዓት ኣኺሉ ባቡር ነቒላ፡
ካብ ምጽዋዕ ዓሰብ ብኣዱሊስ ዙላ፡
ወለላ መዓር ማዕድንና ሓዚላ።

ላለይ ላሎ/2/፡
ወደባት ዓደይ የዛርበኒ’ሎ
ንዕናይ ምሳይ ኣንቲ ወለሎ፡
ወደባት ዓደይ የዛርበኒሎ

ላለይ ላሎ/2/፡ ማርሳ ተኽላይ ይረኣየኒ’ሎ፡
ላለይ ላሎ/2/ ማርሳ ፋጥማ የዛርበኒሎ
ላለይ ላሎ/2/፡ ወደባት ዓደይ ይረኣየኒ’ሎ፡
ላለይ ላሎ/2/ ወደባት ዓደይ የዛርበኒ’ሎ


ኣብ'ዛ ግጥሙ "ወደባት" ኪብል ከሎ በቲ ሓደ ሸነኽ ነቲ ግዑዝ ኣብ ገምገም ባሕሪ ዚርከብ መራኽብ ዝዕሸጉሉ ክፋል ባሕርና ከስምዕ ከሎ፡ "ወደባት" ዚብል ቃል ብካልእ ሸነኽ "ወዲ ሃገር" ወይ "ወዲ ዓዲ" ንምባል ክንጥቀመሉ ንኽእል'ዶ? ተመራመርቲ ምስ ተመራመርኩም ቀስ ኢልኩም ትነግሩና ትኾኑ ግዲ! ኣብ ቀጻሊ ብካልእ ትሕዝቶ ግጥሚ ናይ ሓንቲ ካብ ዜማታቱ ዬራኽበና!
:mrgreen:

Meleket
Member
Posts: 3057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: Re: ስነፍጥረትን ለማነጋገር የበቃ ኤርትራዊ የጥበብ ሰው - የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) - በስንኞቹ ሲዘከር

Post by Meleket » 16 Sep 2023, 03:58

የድሃ ኣባት እየተባለ በህዝብ ዘንድ አክብሮት የተቸረው የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) ስነፍጥረትን ለማነጋገር በቅቷል ስንል፡ ከዋክብትን፡ ጨረቃንና ጸሓይን ስላነጋገረ ብቻ ሳይሆን፤ የኤርትራን ወደቦችንም ጭምር ለማነጋገር ስለበቃም ነው። “ያገሬ ወደብ፡ ዝምብሎ እያናገረኝ ነው እያዋራኝ ነው” በማለት፡ ወደብን ያህል ግዑዝ ኣካል ዝም ብሎ የሰው ልጅን ማናገርና ማነጋገር እንደሚችል ፍንትው አድርጎ አሳይቶናል፤ በጥበባዊ ስራው።

የግጥሙ “ግድፍ ትርጉምና ይዘት” እንደሚሳየን፤ ዋንኛ መልእክቱ ኤርትራዉያንን በሙሉ ለትግል ማነሳሳት ነው። ያኔ ለጋውና ወጣቱ ድምጻዊ የማነ፡ እዬተኮላተፈም በሚያዜማቸው ዜማዎቹ የህዝብን ልብ ኣንጠልጥሎ ይዞ እንደነበር፡ ብዙዎች ይስማሙበታል። በወቅቱ የኤርትራ ማዕድን ከድባርዋና ከመሳሰሉት ስፍራዎች ኢትዮኒቦን በተባለ ኩባንያ ሊበዘበዝ ጀምሮ፡ ይህን መሰሉ የየማነ ሙዚቃ ባነሳሳው የትግል መንፈስ የሚንቀሳቀሱት የነጻነት ታጋዮች፡ የማዕድኑን ስፍራ በማጋዬት፡ የኤርትራ ህዝብ አንዳችም ጥቅም የማያገኝበትን የሃብት ብዝበዛ አስተጓጉለው፡ ጭራሹኑም በኃይል እርምጃቸው አስገድደው እንዲቋረጥ እንዳደረጉም በሰፊው ይታወቃል።

ግጥሙ ውስጥ “ወደባት” የሚለው ቃል ባንድ በኩል “ወደቦችን” ሲያመለክት፡ በሌላ በኩል ደግሞ “ያገር ልጅ”፣ ‘ባለ ሃገር’ ማለትም “መሃል ሰፋሪና መጤ ያልሆነም” እንደማለት ሊያገለግል ይችላል ብለንም ጠርጥረናል ። ባርያ በቅኒያዊ መንገድም ያገሬ ሰዎች እያናገሩኝ ነው፡ የወደቦቻችን ሁኔታ አነጋጋሪ ነው፥ በወደቦቻችን በኩል ያገራችንን ጸጋ እያጋበሱ እየወሰዱት ነው። አንቺም እቴ፡ ኣንተም ወንድሜ አንድ መላ እናብጅ እያለ እንዳንጐራጐረ ነው ህዝቡ የሚረዳው።

https://www.youtube.com/watch?v=u1KPsMN0NWs
https://www.youtube.com/watch?v=2CZJUdft1gg

የዚህን ወርቃማ ኤርትራዊ የባህር ዕንቁና የጥበብ ፈርጥ የባርያን ግጥም ‘ግርድፍ ትርጉም’ ከነ ቅመሙ እነሆ

ወደቦቼ

ላለይ ላሎ፡/2/
“ኣናገረኝ” እኮ ወደቤ “ዝም ብሎ”፡
ያገሬ ወደብ ታዬኝ ፍንትዉ ብሎ።


እስቲ ኑ እንሂድ በዚህ ጫፍ በኩል፡
ያገሬን ወደቦች እንኳላቸው ኩል።

በስመኣብ ብዬ ልጀምር ሙዚቃ፡
ቀልቤ እናንተው ላይ ትታይ ደማምቃ፡
ወደቦቸ እያልኩ እቀውጣለሁ፡
ምን እንዳላቸው በደንብ ኣውቃለሁ።


ላለይ ላሎ/2/፡
እያዋራኝ ነው ወደቤ ዝም ብሎ።

ምጽዋና ዓሰብ ኣዱሊስም ዙላ፡
ለዳህላክና ናኩራ ደሴቶቸ ሁላ፡
ሰላም እያልኩኝ እስክንገናኝ ኋላ፡
ከዚሁ ልላክ የናፍቆቴን መሃላ።

ላለይ ላሎ/2/፡
እያዋራኝ ነው ወደቤ ዝም ብሎ።
ላለይ ላሎ/2/፡
አነጋገረኝ ወደቤ ዝም ብሎ፡
በጽሞና መሃል ድምጽ ያለው መስሎ።


ነይ ከኔ ጋራ የኔ መለሎ፡
የወደቡን ድምጽ እንስማ ቶሎ።
ነይ ከኔ ጋራ የኔ ወለላ፡
የወደቡን ጉዳይ በጋራ እናስላ።

መርከብ ተነሳ ሰዓቱ ደረሰ፡
በምጽዋ አድርጎ ዓሰብ ገሰገሰ፡
አዱሊስና ዙላ እያተራመሰ፡
ያገሬን ማዕድናት አግበሰበሰ።

ሰዓቱ ደርሶ ቧቡር ተነስቷል፡
የሃገሬን ሃብት ተሸክሞታል፡
ከምጽዋ ዓሰብ በኣዱሊስ ዙላ፡
ሲያጋብስ ኣየነው ሃብቱን በሞላ።

ላለይ ላሎ/2/፡ እያዋራኝ ነው ወደቤ ዝም ብሎ፡
ላለይ ላሎ/2/፡ ነይ ማርሳ ተኽላይ እንሂድ ቶሎ።
ላለይ ላሎ/2/፡ ነይ ማርሳ ፋጥማ እንሂድ ቶሎ።
ላለይ ላሎ/2/፡ አነጋገረኝ ወደቤ ዝም ብሎ።


https://www.youtube.com/watch?v=VyQH2ZYL6us

በቀጣይ ክፍል፡ የማነ ካንጎራጎራቸው ሙዚቃዎች የአንዱን ርእስ አንስተን ደግሞ ስንኞቹን በመጋራት የግጥሙን ይዘት በጋራ በመካፈል ይህን ዕንቝ ኤርትራዊ ሃብታችንን እንዘክራለን።

ይህ ድንቅ ኤርትራዊ የጥበብ ሃዋርያ ወደዚያኛው ዓለም ካለፈ 25 ዓመታት አስቆጥሯል፡ ገና በለጋ እድሜው በሚልዮኖች ልብ ውስጥ የሰፈረ የጥበብ ሰው በመሆኑ፤ ኤርትራውያን እዬዘከሩት ይገኛሉ። ሙዚቃውን ለሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ ስናስተዋውቅም፡ የጥበብን ሚና እንዲሁም የጥበብን ርቀትም ለጥበብ አፍቃሪዎች ለማጋራት ካለን ልባዊ መሻት በመነሳሳት ነው። እርግጥ ነው ይህና ይህን መሰሉ ጽሑፍ ለያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ተማሪዎችና መምህራን ለኢትዮጵያውያን የሙዚቃ ሰዎችም አንድ መልእኽትን እንደሚያስተላለፍ፡ እኛ ኤርትራዉያን የመሃልና የመስመር ዳኞች በኤርትራዊ ጭዋነት ኩራትና ትህትና ጭምር እናምናለን። ማን ያውቃል ኣንድ ቀን ኣንድ ጥበብ አፍቃሪ ኢትዮጵያዊ ተነስቶም የየማነን የፍቅር ዜማዎች ከነ ሙሉ ይዘቱ ባማርኛም ሲያንጎራጉር እንሰማ ይሆናል።
:mrgreen:

Meleket
Member
Posts: 3057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: Re: ስነፍጥረትን ለማነጋገር የበቃ ኤርትራዊ የጥበብ ሰው - የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) - በስንኞቹ ሲዘከር

Post by Meleket » 25 Sep 2023, 04:18

ብርግጽ ካብ ልቢ የማነ ባርያ ንዝፈልፈሉ ግጥምታትን ዜማታትን ዝያዳ ሕይወት ዚዘርኡሉ ሙዚቀኛታት ከምዝዀኑ ንምርኣይ እዚኣ ብዛዕባ ስደት ዘዜማ ዜማ ህያው ምስክር እያ። ጊታሪስት ማዕረ የማነ ንጊታሩ ሰቆቓዊ ዜማ ከምተፈልፍል ጌሩ’ሎ፡ ካልኦት’ውን ከምኡ።

ብዛዕባ ስደት ካብ ተዘርበ፡ አብ ሱዳን ያኢ የማነ ብስደት ነቢሩ ኔሩ። ሽዑ ኣዲኡ ክርእይኦ ከይደን። አብቲ ብርቱዕ ድርቂን ጥሜትን ዝነበሮ ግዜ፡ የማነ “መሸማዕ ምሉእ ሽኾርን ማይን” ንዝዀነ ጥሙይ ንምዕንጋል ኣብ ኣፍ ደገ ገዝኡ የቀምጥ ነቢሩ። አደ ገሪምወን ንሰበይቱ “ኣንቲ ጓለይ እንታይ ኢየ ዝርእይ ዘለኹ፡ ነዚ መሸማዕ ሽኾር በጃኺ ኣብ ገዛ ኣእትይዮ” ይብላ፤ መለሰት ሰይቲ የማነ “ማማ ነዚኣ መሸማዕ ሽኾር ናብ ገዛ እንተእቲናያ፡ የማነ ካልእ መሸማዕ ምሉእ ሽኮር ገዚኡ ኣብኣ ከንብር ኢዩ!” ከምዚ’ዩ ልግሲ ወዲ ሃገር ብርግጽ ኣቦ ድካታት የማነ ‘አምባሳደር ህዝቡ”።

ሕጂ ናብ ምስትምቃር ግጥሚ የማነ። ስደት ሕጂ ኣይኰነን ጀሚሩ፡ ዓመጽ ሕጂ ኣይኰነን ጀሚሩ፡ ቀደም ኢዩ ሰብ ከይሰልጠነ ከሎ፡ እጂ’ውን ኣብ ዘይሰልጠነ ዓለም ስደት ይቕጽል ኣሎ። ቀደም ኣብ ግዜ መግዛእቲ ስደት ነቢሩ። ሕጂ’ከ? ዬማነ እንተዝህሉ ኔሩ በግጥምን ዜማን ኣዋዲዱ ምመለሰለና ነቢሩ። ዓመጽን ምዝመዛ ሰብን መግዛእትን እንከይተኣለየ፡ ስደት ኣየብቕዕን እናበለ የማነ በዛ ትንቢታዊትን ሰቆቃዊትን ዜማኡ መብርሃልና ነቢሩ። ሕጂ ናብ ምስትምቓር

https://sonichits.com/video/Yemane_Bary ... he_Yu_Sdet

ስደት

ሎሚ ኣይኮነን ሓዲሽ ተጀሚሩ ስደት፡
ውግእ ወረ ውግእ ጸረሰላም ሁከት፡
ዝጸንሀ ኢዩ ካብ ቀደም ዓለም ምስተፈጥረት፡
ሰብ ከይሰልጠነ ከሎ ገና ኣብ ድሕረት።


ይሽየጥ እውን ኔሩ’ዩ ወዲ ሰብ ብዋጋ፡
ብመቑሕ ተቋሪኑ ሚዛን ዓጽመ ስጋ፡
ምልኪ ጐይታ ኮይኑ ወሪዱ ዕዳጋ፡
ስለዚ ቀደምዩ ዓለም ከይማዕበለት፡
ካብ ሽዑ ከኣ’ያ ሰላም ዘይነበረት።

ሎሚ’ውን እንተኰነ ኣብ’ቲ ምዕቡል እዋን፡
ዓመጽ ኣይተረፈን ዘይናትካ ምውናን።
ስለዚ’ዩ ከኣ ስደት ዝቀጸለ፡
ካብ መግዛእቲ ክሃድም ዝዓመረ።


ሓድሓደ ግዜ ኩናት መጸውዒ ሰላም ኢዩ፡
ናይ መግዛእቲ ሕቶ መፍትሒኡ ቅልጽም ኢዩ፡
ናይ ጭቁናት ቃልሲ ዕምሩ ኣይጠፍእን እዩ፡
ኣይርከብን እውን ሰላም ለሚንካ ብዋዛ፡
መግዛእቲ ከይጠፍአ ሰብ ብሰብ ምዝመዛ።


ጨቋንን ተጨቋንን መግዛእቲ ከይተኣልየ፡
ዘበት ኢዩ ክትርከብ’ታ ናይ ሰላም ስየ።

ኣይርከብን እውን ሰላም ለሚንካ ብዋዛ፡
መግዛእቲ ከይጠፍአ ሰብ ብሰብ ምዝመዛ።


ንሎሚ ብምኽንያት ዓለማዊ መዓልቲ ስደተይናታት ነዚ ካብ ኣስተማቐርና፡ ኣብ ቀጻሊ ብካልእ ግጥሚ የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) ኣብ ምስትምቓር ዬራኽበና።
Last edited by Meleket on 25 Sep 2023, 10:42, edited 2 times in total.

Digital Weyane
Member+
Posts: 8549
Joined: 19 Jun 2019, 21:45

Re: ስነፍጥረትን ለማነጋገር የበቃ ኤርትራዊ የጥበብ ሰው - የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) - በስንኞቹ ሲዘከር

Post by Digital Weyane » 25 Sep 2023, 06:45

ተወዳጁ ኤርትራዊ አቀንቃኝ የማነ ባርያ ፣ ባንዳው የሕወሃት አሸባሪ ቡድን <<ኡኡኡ ጆ ባይደን>> እና <<ኽራይሚያ ኾይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ>> ብሎ እየጮኸ ራሱ በቆፈረው ከርሰ መቃብር ውስጥ እንደሚገባ ተተንብዮ ነበር። ትንቢቱ ተፈፀመ! አምየን። :roll: :roll:

Meleket
Member
Posts: 3057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ስነፍጥረትን ለማነጋገር የበቃ ኤርትራዊ የጥበብ ሰው - የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) - በስንኞቹ ሲዘከር

Post by Meleket » 25 Sep 2023, 10:52

የማነ "ተተንብዮ" ነበር ወይስ የማነ "ተንብዮ" ነበር? ብሔራዊ ቋንቋህን ጠንቅቀህ ማወቅ ይጠበቅብሃል ወዳጃችን! :mrgreen:
Digital Weyane wrote:
25 Sep 2023, 06:45
ተወዳጁ ኤርትራዊ አቀንቃኝ የማነ ባርያ ፣ ባንዳው የሕወሃት አሸባሪ ቡድን <<ኡኡኡ ጆ ባይደን>> እና <<ኽራይሚያ ኾይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ>> ብሎ እየጮኸ ራሱ በቆፈረው ከርሰ መቃብር ውስጥ እንደሚገባ ተተንብዮ ነበር። ትንቢቱ ተፈፀመ! አምየን። :roll: :roll:

Meleket
Member
Posts: 3057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: Re: ስነፍጥረትን ለማነጋገር የበቃ ኤርትራዊ የጥበብ ሰው - የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) - በስንኞቹ ሲዘከር

Post by Meleket » 26 Sep 2023, 04:36

ጊታር ወዳዶች ይህቺ ዜማ እንዳታመልጣችሁ . . . .

በተለያየ ምክንያት ወደ ተለያዩ ሃገሮች የተሰደዱ እልፍ ኣእላፍ ኢትዮጵያውያን ይቺን የየማነ ባርያ ዜማ ከነግጥሟ ለማጣጣም እድል ካገኙ፡ የኤርትራ ህዝብ የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ)ን ለምን እንደሚወደው ፍንትው ብሎ ይታያቸዋል። የማነና በዚህች ዜማው ውስጥ የተሳተፉ ሙዚቀኞች ምን ያህል ከሱ ሓሳብ ጋር እንደተጣጣሙ ለማዬት የጊታሪስቱን ቁዘማ በመስማት ለመመስከር ይቻላል።

የማነ በግጥሙ እንዳብራራው ስደት አሁን አይደለም የጀመረው፡ ብዝበዛ፡ የሰውን መመኘት፡ በሃይል ብቻ የማመን የጡንቸኞች ኣባዜ ወዘተ ከጥንት የነበረ ነው፡ ገና የሰው ልጅ ሳይሰለጥን። አሁንም ባልሰለጠኑት ህዝቦች መካከል ይህ እኩይ ተግባር ስላለ፡ ስደትም ቀጥሏል። ስደት የሚያቆመው ጨቋኝና ተጨቋኝ የሌለበት ሁኔታ በትግል መጐናጸፍ ሲቻል ብቻ ነው ይለናል፡ ሰላምም በልመና ሳይሆን በትግል እንደምትገኝም ግልጽ አድርጎልናል ነብዩ የማነ ባርያ።

https://sonichits.com/video/Yemane_Bary ... he_Yu_Sdet

ስደት

ዛሬ ገና ኣይደለም የጀመረው ስደት፡
እርስበእርስ ውጊያና ጭካኔና ሁከት፡
ከጥንት የቆዬ ነው ዓለም ስትፈጠር፡
ገና ሳይሰለጥን ሰው ሳለ ኋላቀር።

ይሸጥም ነበረ የሰው ልጅ በዋጋ፡
ታስሮ በሰንሰለት ተመዝኖ ስጋ።
አጥንትና ስጋ ወርደው ወደ ገበያ፡
ለጭካኔያችን ጥግ ሆነዋል መታያ።

ከጥንት ከጥዋቱ ዓለም ሳትሰለጥን፡
ያኔ ጀምሮ ነው ሰላም የጠፋችን።

አሁን በዚህ ዘመን በስልጡኑ ግዜ፡
የሰውን መቀማት የኃይለኛ አባዜ፡
ኣልቀረም ገና ኣለ፡ ይሻዋል ኑዛዜ።
ስለሆነም ስደት አሁንም ቀጥሏል፡
ከግፈኞች ሽሽት ይበልጥ ተፏፉሟል።

አንዳንዴ ጦርነት ሰላምን ይጠራል፡
ጡንቻ ሲተባበር ገዢን ይዘርራል።
የጭቁኖች ትግል በፍጹም አይጠፋም፡
ጦርነትን አልፋ ትመጣለች ሰላም።

ሰላም አትገኝም በመለማመጥ፡
ሰው እስካላቆመ የሰው ደም መምጠጥ፡
በሃሳብ ተባብሮ በዝባዥን መዘርጠጥ።

ሰላም አትገኝም በመሞዳሞድ፡
ሰው እስካላቆመ የሰው ስጋ መጎመድ፡
ኃይልን አስተባብሮ ገዥን ማርበድበድ፡
ግፈኛን ደርምሶ በኃይል መናድ።

ጨቋኝና ገፊ፡ ገዢ ኃይል ሳይጠፋ፡
የሰላም ዘንባባ ኣትበቅልም በተስፋ፡
የሰላም ዘንባባ ኣትመጣም በተስፋ።


ሱዳን ውስጥ የማነ በስደት ይኖር በነበረበት ወቅት፡ ወላጅ እናቱ ሊያዩት ወደ ሃገረ ሱዳን ያመራሉ። ወቅቱ ብርቱ ረሃብና ድርቅ የነበረበት ግዜ ነበር። እህልም ስኳርም ያኔ እጅግ ተወዶ ነበር ኣሉ፡ ታድያ ዬዋሁ የማነ ጆንያ ሙሉ ስኳርና ውሃ ቤቱ በራፍ ላይ ያስቀምጣል። ማንም ኣላፊ ኣግዳሚ የተራበና የተጠማ ዜጋ ስኳሩን እየበጠበጠ እንዲጠጣው መሆኑ ነው። ታድያ እናቱ ይሄን ጆንያ ሙሉ ስኳር በራፋቸው ደጅ ላይ መተውን በማዬት፡ ለሚስቱ “ልጄ እባክሽ ይህን ጆንያ ሙሉ ስኳር ወደ ቤት ውስጥ አስገቢው፡ ለምን በራፍ ላይ በጸሃይና ንፋስ ይሰጣል” ይላሉ። የየማነን ባህርይ ጠንቅቃ የምታውቀው ሚስቱ ሃረገወይንም “ኣዬ እማማ፡ ይህችን ጆንያ ስኳር ወደ ቤት ካስገባኋት፡ የማነ ሌላ ጆንያ ስኳር ገዝቶ እዛችው ቦታ ላይ ያስቀምጣል!” እንዲህ ነው የማነ ባርያ፡ የመስጠት ምሳሌ በመሆን በኤርትራውያን መካከል ሁሌም የሚዘከረው።

የዓለም የስደተኞች ቀን ምክንያት በማድረግ ይህንን ከተካፈልን ዘንዳ፡ በቀጣይ ደግሞ ከዜሞቹ የኣንዷን ግጥሞች እንካፈላለን።

Meleket
Member
Posts: 3057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: Re: ስነፍጥረትን ለማነጋገር የበቃ ኤርትራዊ የጥበብ ሰው - የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) - በስንኞቹ ሲዘከር

Post by Meleket » 04 Apr 2024, 02:28

የማነ ገብረሚካኤል (የህዝቡ ባርያ ወይም አገልጋይ)፡ ላገሩ ልጅ አፍሪካዊ የቆዳ ቀለም ያንጐራጐረአው መሆኑ ነው። ስነጥበብ አፍቃሪዎች ሙዚቃዉን ፈተሽ ፈተሽ አድርጋቹ አጣጥሙት። የግጥሙን ይዞታ ግን እኛ ኤርትራውያን የመሃልና የመስመር ዳኞች፡ በኤርትራዊ ጭዋነት ኩራትና ትህትና ጭምር አጋርተናችኋል። :mrgreen:
ጓል ሃገረይ

ብርዒ ስገም ኣፃብዕታ ሣዕሪ ለይለይ፡
ክሣዳ መሶብ ሽንጣ ጸጉራ ሃረይ፡
መሪጸያ ኣሎኩ ጓል ሃገረይ፡
ደቂ ዓድና ዕልል በላለይ።

ዓይና ፍሩይ ክቡር ዕንቝ ባሕሪ፡
ግርማ ጸልማት ወርሒ ጸሃይ ቀትሪ፡
ገጻ ብሩህ ምስናይ ፍሽኽታ፡
ጓል ሃገረይ የብላን መሰታ።

ተፈታዊ ሕብሪ ኣፍሪቃዊ ቆርበት፡
መረጽኹኺ ኣነ ፈተኹኒ ኣነ፡
መረጽኹኒ ኣነ ንሓዳር ንክብረት፡
ፈተኹኺ ኣነ መረጽኹኒ ኣነ፡
ፈተኹኺ ኣነ ንሓዳር ንኽብረት።


ብርዒ ስገም ኣፃብዕታ ሣዕሪ ለይለይ፡
ክሣዳ መሶብ ሽንጣ ጸጉራ ሃረይ፡
መሪጸያ ኣሎኩ ጓል ሃገረይ፡
ደቂ ዓድና እስከ መርቑለይ።

ከናፍራ ዘቢብ ተኽሊ ወይኒ፡
ማይ ናይ ንግሆ ንጹሕ ጻዕዳ ስኒ፡
ፍረ ሮማን ጽቡቓት ምዕጕርታ፡
ዓርከብኮባይ ሃለንጋይ ቁመታ፡
ብርቱካን ዮም ጽቡቓት ምዕጉርታ፡
ዓርከብኮባይ ሃለንጋይ ቁመታ።

ተፈታዊ ሕብሪ ኣፍሪቃዊ ቆርበት፡
መረጽኹኺ ኣነ ፈተኹኒ ኣነ፡
መረጽኹኒ ኣነ ንሓዳር ንክብረት፡
ፈተኹኺ ኣነ መረጽኹኒ ኣነ፡
ፈተኹኺ ኣነ ንሓዳር ንኽብረት።

ብርዒ ስገም ኣፃብዕታ ሣዕሪ ለይለይ፡
ክሣዳ መሶብ ሽንጣ ጸጉራ ሃረይ፡
መሪጸያ ኣሎኩ ጓል ሃገረይ፡
ደቂ ዓድና ሰላም በሉለይ።

ታይ ዝበለ መልክዕ ታይ ዝበለ ቁንጅና፡
ኣቤት እወ ጠባይ ህያውነት ልቦና።
ያገሬ ልጅ

ጣቶቿ ያማሩ እንደ ገብስ ዘለላ፡
ጸጉሯ ሃር የሆነ ኣንገቷ ሙዳዬ- ኣለላ፡
መርጫለው እኔ የሃገሬን ልጅ፡
ዕልል በሉልን ፍቅርን እናውጅ።

ቦግ ያሉት ኣይኖቿ የባህር ዕንቁዎች፡
ጨረቃና ጸሓይ ጨለማን ኣብሪዎች።
ብሩህ ፊቷ የሞላ ፈገግታ፡
የሃገሬ ልጅ ለህሊና እርካታ፡
ወደርስ የላትም ልዩ ነው ውበቷ።

አፍሪቃዊ ውበት የቆዳዋ ቀለም፡
እኔ እሷን ወደድኩኝ እስከ ዘለዓለም።
እኔ አንቺን መረጥኩኝ ለትዳር አጋሬ፡
መድሃኒቴ ኣንቺ ነሽ የፍቅር መምህሬ።


ጣቶቿ የመሰሉ የገብስ ዘለላ፡
ጸጉሯ ሃር የሆነ ኣንገቷ ሙዳዬ- ኣለላ፡
የሃገሬን ቆንጆ እኔ መርጫለሁ፡
መርቁልኝ በሉ እኔ እሷን ብያለሁ።

ከንፈሮቿ ናቸው የወይን ዘለላ፡
ኩልል ያሉ ውሃ ጥርሶቿ በሞላ፡
ጉንጯቿ ቆንጆችዎች የዘይቱን ፍሬ፡
ይህችን መለሎ ታድዬ ማፍቀሬ፡
ጉንጯቿ ቆንጆችዎች የዘይቱን ፍሬ
ይህችን ጠምበለል ታድዬ ማፍቀሬ።

ውብነው አፍሪቃዊ የቆዳዋ ቀለም፡
እኔ እሷን ወደድኩኝ እስከ ዘለዓለም ።
እኔ አንቺን መረጥኩኝ ለትዳር አጋሬ፡
መድሃኒቴ ኣንቺ ነሽ የፍቅር መምህሬ።

ጣቶቿ የመሰሉ የገብስ ዘለላ፡
ጸጉሯ ሃር የሆነ ኣንገቷ ሙዳዬ- ኣለላ፡
የሃገሬን ቆንጆ እኔ መርጫለሁ፡
ሰላምታ ኣድርሱልኝ እኔ እሷን ብያለሁ።

ምን ዓይነት መልክ ነው፡ ምን ዓይነት ቁንጅና፡
ኣሟልቶ ሰጥቷታል ጠባይ ከልቦና።

Post Reply