የኢትዮጵያ ኦሮቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ሲኖዶስ ዛሬ ለትግራይ ህዝብ ባቀረበው የይቅርታ ደብዳቤ: ይቅርታ እንዲጠይቅ እንደ ምክንያት ካስቀመጣቸው ነጥቦች አንዱ እንዲህይ ይላል "ጦርነቱ እንዲቆም በወቅቱ መግለጫ ባለመሰጠቷ"
እኛ እያልን ያለነው ደግሞ:
ዋናው ችግር የኢትዮጵያ ኦሮቶዶክስ ቤተክርስትያን "ጦርነቱ እንዲቆም በወቅቱ መግለጫ ባለመሰጠቷ" ሳይሆን፤ ጦርነቱ በይፋ መደገፏ ነው። የደገፈችበት መረጃ እኮ በየኢንተርኔቱ በዜና መልክ አለ ማንንም ማታልል አይቻልም።
"የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን "ከ ሀገር መከላከያ ጎን እንቆማለን" በሚል ለሰራዊቱ ያላት ድጋፍ ገለጸች። "ከ ሀገር መከላከያ ጎን እቆማለን" በሚል መሪ ቃል የተላለፈው ጥሪ በመቀበል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት ለመከላከያ ሰራዊቱ ያለውን ድጋፍ ገለጸ..." የ EBC ዜና! (November 17, 2020)!
ምንጭ
https://shorturl.at/fsvxS
እውነት መናገር እና መቀበል ያስፈልጋል። እውነትን በመደፍጠት ፍትህ እና ይቅርታ ሊገኝ አይችልም
- ጦርነቱ እንዲቆም በወቅቱ መግለጫ ባለመሰጠቷ፣
- በጦርነቱ መካከል ወደ ትግራይ ክልል መግባትና መውጣት በሚቻልበት ወቅትም በክልሉ የሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንንና መላው #ሕዝበ_ትግራይን በአካል በቦታው ተገኝታ ባለመጠየቋና ባለማጽናናቷ፣
- ጦርነቱ ቁሞ በአገር አቀፍ ደረጃ እርቀ ሰላም ከወረደበት ጊዜ ጀምሮ ለደረሰው ጉዳት በቅዱስ ሲኖዶስ የተወሰነውን ሰብአዊ ድጋፍ በውሳኔው መሠረት በወቅቱ ማድረስ ባለመቻሏ፣
በዚሁም የተነሣ በቤተ ክርስቲያኗና በመላው ሕዝበ ትግራይ መካከል ለተፈጠረው ቅሬታና አለመግባባት ቅዱስ ሲኖዶስ በይፋ ይቅርታ ጠይቋል።
=========|||||||||||||||||||||||||||||||
የ ዮም ፖስት መልእክት:
ጅምሩ ባይከፋም የኢትዮጵ ኦሮቶዶክስ ቤተክርስትያን በትግራይ ህዝብ ላይ ያደረሰችው ግፍ እንዲሁ በቀላሉ በይቅርታ ብቻ የሚታለፍ አይደለም። ምክንያቱም:
(ሀ): የኢትዮጵያ ኦሮቶዶክስ ቤተክርስትያን "ጦርነቱ እንዲቆም በወቅቱ መግለጫ ባለመሰጠቷ" ሳይሆን መባል ያለበት፤ ጦርነቱ በይፋ በመደገፏ መባል አለበት!
"ከ ሀገር መከላከያ ጎን እቆማለን" በሚል መሪ ቃል የተላለፈው ጥሪ በመቀበል የኢትዮጵያ ኦሮቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት ለመከላከያ ሰራዊቱ ያለውን ድጋፍ ገለጸ! (November 17, 2020)!
https://shorturl.at/DJRT1
(ለ): የኢትዮጵያ ኦሮቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ሲኖዶስ ብውስጧ የተሰገሰጉ ጥላቻ እና ጦርነት ሰባኪ ጳጳሳት ይዛ እስከቀጠለች ድረስ፣ ማንም የሚያከብራት እና seriously የሚወስዳት ሰው አይኖሮም። በከፍተኛ ደረጃ ጥላቻ እና ጦርነት የሰበኩ የሲኖዶስ አባላት የሆኑ ጳጳሳት:
1. "አንድ አምስት መቶ ሺህ (500,000) የሚሆኑ የወያኔ ካድሬዎች እና ደጋፊዎች ፈርተው ሄደዋል እንጂ የተፈናቀለ የለም። ... አክሱም ላይ ሰው ተገደለ የሚባለው፣ አንድም ሰው ሲናገር አልሰማሁም። ውጭ ያሉ የሚያራግቡት ነው" የሲኖዶስ አባል አቡነ ጴጥሮስ! Video
https://www.facebook.com/YomePost/video ... 424505889/
"ቤተክርስትያን ጦርነቱ ለምን አላወገዘችም ይላሉ፤ ምኑ ነው የምታወግዘው? ጦርነቱ የከፈተው እኮ ህወሓት ነው።" የሲኖዶስ አባል አቡነ ጴጥሮስ! Video
https://www.facebook.com/fitwi.meles/vi ... 3870582735
"ህወሃት ተመልሶ ይመጣል ብላችሁ አትጠብቁ። ይህ መርዶ ነው። ህወሓት ተመልሶ አይመጣም ቁርጣችሁን እወቁ" የሲኖዶስ አባል አቡነ ጴጥሮስ! Video 3
https://www.facebook.com/10000108560522 ... 8731346843
2. "ሰይጣን ቢገዛን ይሻላል..." የሲኖዶስ አባል ኣቡነ ሚካኤል!
Video
https://www.facebook.com/ermias.haile.5 ... 9429656622
3. "ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ ያሰኛት እኮ አማራ ነው። ዋልድባ የማን ነው? ዋልድባን አስረክበህ እዚ ቁጭ ብለህ ጠላ እየጠጣህ ወሬ ማውራት ምን ይጠቅመሃል? ... ክላሽ ያዝ ... ከውስጣችሁ ጁንታዎች አሉ መሰለኝ ... " የሲኖዶስ አባል አቡነ መቃርዮስ!
Video
https://shorturl.at/jBLOP
4. "አቡነ ማትያስ የትግራይ ህዝብ እንዲኖር አልተፈቀደለትም ሲሉ ሰማሁዋቸው፤ በጣም አዘንኩኝ፣ ተሸማቀቅኩ። . . . ከህወሓት ጋር መናጋገር አያስፈልግም..." የሲኖዶስ አባል ኣቡነ ፋኑኤል!
https://shorturl.at/qAIN1
5. "የአቡነ ማትያስ ንግግር ቤተክርስትያን አይወክልም" በማለት አቡነ ማትያስ እንዳይናገሩ ማይክ የቀሟቸው የሲኖዶስ አባል አቡነ ዮሴፍ!
https://www.facebook.com/watch/?v=730609234301793
6. በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ቤተክርስትያን ሲያገለግሉ የነበሩ ተጋሩ፣ በማንነታቸው ምክንያት እንዲታሰሩ እና ከ ስራቸው እንዲባረሩ ያደርጉ የሲኖዶስ አባል ኣቡነ መልከጼዲቅ።
https://shorturl.at/eLMQT
.
.
.
ሌሎች ጻጻሳትም አሉ።
እውነት መቀበል ያስፈልጋል። ከዛ በይቅርታ የሚታለፍ ጥፋት በይቅርታ ይታለፋል፣ የሚያስቀጣ ጥፋት ከሆነ ደግሞ ተገቢ ቅጣት መስጠት ያስገልጋል። ያለ እውነተኛ ፍትህ እውነተኛ ይቅርታ ሊገኝ አይችልም!
Please wait, video is loading...